ምሳሌ 20 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 20:1-30

1የወይን ጠጅ ፌዘኛ፣ ብርቱ መጠጥም ጠበኛ ያደርጋል፤

በእነዚህ የሳተ ሁሉ ጠቢብ አይደለም።

2የንጉሥ ቍጣ እንደ አንበሳ ግሣት ነው፤

የሚያስቈጣውም ሰው ሕይወቱን ለመከራ ይዳርጋል።

3ከጠብ መራቅ ለሰው ክብሩ ነው፤

ተላላ ሁሉ ግን ለጥል ይቸኵላል።

4ሰነፍ ሰው በወቅቱ አያርስም፤

ስለዚህ በመከር ወራት ይፈልጋል፤

አንዳችም አያገኝም።

5የሰው ልብ ሐሳብ እንደ ጥልቅ ውሃ ነው፤

አስተዋይ ሰው ግን ከዚያ ቀድቶ ያወጣዋል።

6ብዙ ሰው ጽኑ ፍቅር እንዳለው ይናገራል፤

ታማኝን ሰው ግን ማን ሊያገኘው ይችላል?

7ጻድቅ ነቀፋ የሌለበት ሕይወት ይመራል፤

ከእርሱም በኋላ የሚከተሉት ልጆቹ ቡሩካን ናቸው።

8ንጉሥ ለፍርድ ዙፋኑ ላይ በሚቀመጥበት ጊዜ፣

ክፉውን ሁሉ በዐይኖቹ አበጥሮ ይለያል።

9ለመሆኑ፣ “ልቤን በንጽሕና ጠብቄአለሁ፤

ንጹሕ ነኝ፤ ኀጢአት የለብኝም” የሚል ማን ነው?

10ሁለት ዐይነት ሚዛን፣ ሁለት ዐይነት መስፈሪያ፣

ሁለቱንም እግዚአብሔር ይጸየፋቸዋል።

11ሕፃን እንኳ ጠባዩ ንጹሕና ቅን መሆኑ፣

ከአድራጎቱ ይታወቃል።

12የሚሰሙ ጆሮዎች፣ የሚያዩ ዐይኖች፣

ሁለቱንም እግዚአብሔር ሠርቷቸዋል።

13እንቅልፍ አትውደድ፤ አለዚያ ድኻ ትሆናለህ፤

ዐይንህን ክፈት፤ የተትረፈረፈ ምግብ ይኖርሃል።

14ዕቃ የሚገዛ፣ “የማይረባ ነው፤ የማይረባ ነው” ብሎ ያራክሳል፤

ሲመለስ ግን በግዥው ይኵራራል።

15ወርቁም አለ፤ ቀዩም ዕንተትረፍርፏል፤

ዕውቀት የሚናገሩ ከንፈሮች ግን ብርቅ ጌጦች ናቸው።

16ለማይታወቅ ሰው ዋስ የሆነውን ልብሱን ግፈፈው፤

ለዘልዛላ ሴት የተዋሰውን በቃሉ ያዘው።

17ሰው በማጭበርበር ያገኘው ምግብ ይጣፍጠዋል፤

በመጨረሻ ግን አፉን ኰረት ሞልቶት ያገኘዋል።

18ምክር ጠይቀህ ዕቅድ አውጣ፤

ጦርነት የምትገጥም ከሆነ መመሪያ ተቀበል።

19ሐሜተኛ ምስጢር ያባክናል፤

ስለዚህ ለፍላፊን ሰው አርቀው።

20አባቱን ወይም እናቱን የሚሰድብ፣

መብራቱ በድቅድቅ ጨለማ ይጠፋል።

21ከጅምሩ ወዲያው የተገኘ ርስት፣

በመጨረሻ በረከት አይኖረውም።

22“ለደረሰብኝ በደል ብድሬን ባልመልስ!” አትበል፤

እግዚአብሔርን ጠብቅ፤ እርሱ ይታደግሃል።

23ሁለት ዐይነት ሚዛን በእግዚአብሔር ዘንድ አስጸያፊ ነው፤

አባይ ሚዛን አይወደድም።

24የሰው አካሄዱ በእግዚአብሔር ይመራል፤

ሰውስ የገዛ መንገዱን እንዴት ማስተዋል ይችላል?

25በችኰላ ስእለት መሳል፣

ከተሳሉም በኋላ ማቅማማት ለሰው ወጥመድ ነው።

26ጠቢብ ንጉሥ ክፉዎችን አበጥሮ ይለያል፤

የመውቂያ መንኰራኵርንም በላያቸው ላይ ይነዳል።

27የሰው መንፈስ ለእግዚአብሔር መብራት ነው፤20፥27 ወይም የእግዚአብሔር መብራት የሰውን መንፈስ ይመረምራል

ውስጣዊ ማንነቱንም ይፈትሻል።

28ፍቅርና ታማኝነት ንጉሥን ይጠብቁታል፤

በፍቅርም ዙፋኑ ይጸናል።

29የጎልማሶች ክብር ብርታታቸው፣

የሽማግሌዎችም ሞገስ ሽበታቸው ነው።

30የሚያቈስል በትር ክፋትን ያስወግዳል፤

ግርፋትም የውስጥ ሰውነትን ያጠራል።

Ketab El Hayat

الأمثال 20:1-30

1الْخَمْرُ مُسْتَهْزِئَةٌ، وَالْمُسْكِرُ صَخَّابٌ، وَمَنْ يُدْمِنْ عَلَيْهَا فَلَيْسَ بِحَكِيمٍ. 2سَخَطُ الْمَلِكِ مِثْلُ زَمْجَرَةِ الأَسَدِ، وَمَنْ يُثِيرُ غَيْظَهُ يُسِيءُ إِلَى نَفْسِهِ. 3مِنْ دَوَاعِي شَرَفِ الْمَرْءِ أَنْ يَتَفَادَى الْخُصُومَةَ، وَالأَحْمَقُ يَخُوضُ مُعْتَرَكَ النِّزَاعِ. 4لَا يَحْرُثُ الْكَسُولُ فِي الْمَوْسِمِ خَشْيَةَ الْبَرْدِ، وَفِي أَوَانِ الْحَصَادِ يَطْلُبُ غَلَّةً فَلا يَجِدُ. 5نَوَايَا قَلْبِ الْمَرْءِ كَمَاءٍ عَمِيقٍ وَالْعَاقِلُ مَنْ يَسْتَخْرِجُهَا. 6كَثِيرُونَ يَدَّعُونَ الصَّلاحَ، أَمَّا الأَمِينُ فَمَنْ يَعْثُرُ عَلَيْهِ؟ 7الصِّدِّيقُ يَسْلُكُ بِكَمَالِهِ، فَطُوبَى لأَبْنَائِهِ مِنْ بَعْدِهِ. 8الْمَلِكُ الْمُتَرَبِّعُ عَلَى عَرْشِ الْقَضَاءِ يُغَرْبِلُ بِعَيْنِهِ الْبَصِيرَةِ الْخَيْرَ مِنْ كُلِّ شَرٍّ. 9مَنْ يَدَّعِي قَائِلاً: إِنِّي نَقَّيْتُ قَلْبِي، وَتَطَهَّرْتُ مِنْ خَطِيئَتِي؟

10الْغِشُّ مَا بَيْنَ أَوْزَانِ وَمَعَايِيرِ وَمَكَايِيلِ الشِّرَاءِ، وَأَوْزَانِ وَمَعَايِيرِ وَمَكَايِيلِ الْبَيْعِ رِجْسٌ لَدَى الرَّبِّ. 11حَتَّى الصَّبِيُّ يَكْشِفُ بِتَصَرُّفِهِ هَلْ عَمَلُهُ نَقِيٌّ وَقَوِيمٌ أَمْ لا. 12اللهُ هُوَ صَانِعُ الأُذُنِ الْمُطِيعَةِ وَالْعَيْنِ الْبَصِيرَةِ. 13لَا تُوْلَعْ بِالنَّوْمِ لِئَلّا تَفْتَقِرَ، اسْتَيْقِظْ وَاعْمَلْ فَتَشْبَعَ خُبْزاً. 14يَقُولُ الْمُشْتَرِي: هَذِهِ بِضَاعَةٌ رَدِيئَةٌ! هَذِهِ بِضَاعَةٌ رَدِيئَةٌ! وَإذَا مَضَى بِها فِي حَالِ سَبِيلِهِ يَشْرَعُ فِي الافْتِخَارِ.

15مَعَ أَنَّ الذَّهَبَ مَوْجُودٌ وَاللَّآلِئَ كَثِيرَةٌ، فَإِنَّ الشِّفَاهَ النَّاطِقَةَ بِالْمَعْرِفَةِ جَوْهَرَةٌ نَادِرَةٌ. 16خُذْ ثَوْبَ الْمَرْءِ الَّذِي ضَمِنَ غَرِيباً، وَارْتَهِنْهُ مِنْهُ، لأَنَّهُ كَفَلَ أَجْنَبِيًّا. 17الْخُبْزُ الْمُكْتَسَبُ حَرَاماً سَائِغٌ فِي حَلْقِ الإِنْسانِ، إِنَّمَا لَا يَلْبَثُ أَنْ يَمْتَلِئَ فَمُهُ حَصىً! 18بِالْمَشُورَةِ تَتَرَسَّخُ الْمَقَاصِدُ، وَبِحُسْنِ الدِّرَايَةِ خُضْ حَرْباً. 19النَّمَّامُ يُفْشِي الأَسْرَارَ، فَلا تُخَالِطْ مَنْ يُكْثِرُ الثَّرْثَرَةَ. 20مَنْ يَشْتِمُ أَبَاهُ أَوْ أُمَّهُ يُطْفِئُ الرَّبُّ سِرَاجَ حَيَاتِهِ فِي الظُّلْمَةِ الْحَالِكَةِ.

21رُبَّ مُلْكٍ يُوْرَثُ عَلَى عَجَلٍ فِي بِدَايَتِهِ، يَفْتَقِرُ إِلَى الْبَرَكَةِ فِي نِهَايَتِهِ. 22لَا تَقُلْ: لأُجَازِيَنَّ مَنْ أَسَاءَ إِليَّ شَرّاً. انْتَظِرْ، فَالرَّبُّ يُعِينُكَ. 23التَّلاعُبُ بِالْمَعَايِيرِ رِجْسٌ عِنْدَ الرَّبِّ، وَمِيزَانُ الْغِشِّ أَمْرٌ رَدِيءٌ. 24خَطْوَاتُ الإِنْسَانِ يُوَجِّهُهَا الرَّبُّ، فَكَيْفَ يُمْكِنُ لِلْمَرْءِ أَنْ يَفْهَمَ طَرِيقَهُ؟ 25شَرَكٌ لِلإِنْسَانِ أَنْ يَتَسَرَّعَ فِي النَّذْرِ لِلرَّبِّ ثُمَّ يَنْدَمَ عَلَى مَا نَذَرَ. 26الْمَلِكُ الْحَكِيمُ يُغَرْبِلُ الأَشْرَارَ، ثُمَّ يَسْحَقُهُمْ بِالنَّوَارِجِ، 27نَفْسُ الإِنْسَانِ سِرَاجُ الرَّبِّ الَّذِي يَبْحَثُ فِي كُلِّ أَغْوَارِ ذَاتِهِ. 28الرَّحْمَةُ وَالْحَقُّ يَحْفَظَانِ الْمَلِكَ، وَبِالرَّحْمَةِ يُدْعَمُ عَرْشُهُ. 29فَخْرُ الشُّبَّانِ فِي قُوَّتِهِمْ، أَمَّا بَهَاءُ الشُّيُوخِ فَفِي مَشِيبهِمْ. 30جُرُوحُ الضَّرْبَاتِ تُنَقِّي مِنَ الشُّرُورِ، وَالْجَلْدَاتُ تُطَهِّرُ أَغْوَارَ النَّفْسِ.