ማቴዎስ 1 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

ማቴዎስ 1:1-25

የኢየሱስ የትውልድ ሐረግ

1፥1-17 ተጓ ምብ – ሉቃ 3፥23-38

1፥3-6 ተጓ ምብ – ሩት 4፥18-22

1፥7-11 ተጓ ምብ – 1ዜና 3፥10-17

1የዳዊት ልጅ፣ የአብርሃም ልጅ የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድ ሐረግ የሚከተለው ነው።

2አብርሃም ይስሐቅን ወለደ፤

ይስሐቅ ያዕቆብን ወለደ፤

ያዕቆብ ይሁዳንና ወንድሞቹን ወለደ፤

3ይሁዳ ከትዕማር ፋሬስንና ዛራን ወለደ፤

ፋሬስ ኤስሮምን ወለደ፤

ኤስሮምም አራምን ወለደ፤

4አራም አሚናዳብን ወለደ፤

አሚናዳብ ነአሶንን ወለደ፤

ነአሶን ሰልሞንን ወለደ፤

5ሰልሞን ቦዔዝን ከረዓብ ወለደ፤

ቦዔዝ ከሩት ኢዮቤድን ወለደ፤

ኢዮቤድ እሴይን ወለደ፤

6እሴይ ንጉሥ ዳዊትን ወለደ።

ዳዊት የኦርዮ ሚስት ከነበረችው ሰሎሞንን ወለደ፤

7ሰሎሞን ሮብዓምን ወለደ፤

ሮብዓም አቢያን ወለደ፤

አቢያም አሣፍን ወለደ፤

8አሣፍ ኢዮሣፍጥን ወለደ፤

ኢዮሣፍጥ ኢዮሆራምን ወለደ፤

ኢዮሆራም ዖዝያንን ወለደ፤

9ዖዝያን ኢዮአታምን ወለደ፤

ኢዮአታም አካዝን ወለደ፤

አካዝ ሕዝቅያስን ወለደ፤

10ሕዝቅያስ ምናሴን ወለደ፤

ምናሴ አሞንን ወለደ፤

አሞንም ኢዮስያስን ወለደ፤ 11ኢዮስያስ በባቢሎን ምርኮ ጊዜ፣

ኢኮንያንንና1፥11 ዮአኪን ማለት ነው፤ 12 ይመ ወንድሞቹን ወለደ።

12ከባቢሎን ምርኮ በኋላ፣

ኢኮንያን ሰላትያልን ወለደ፤

ሰላትያልም ዘሩባቤልን ወለደ፤

13ዘሩባቤል አብዩድን ወለደ፤

አብዩድ ኤልያቄምን ወለደ፤

ኤልያቄም አዛርን ወለደ፤

14አዛር ሳዶቅን ወለደ፤

ሳዶቅ አኪምን ወለደ፤

አኪምም ኤልዩድን ወለደ፤

15ኤልዩድ አልዓዛርን ወለደ፤

አልዓዛር ማታንን ወለደ፤

ማታን ያዕቆብን ወለደ፤

16ያዕቆብ ዮሴፍን ወለደ፤ ዮሴፍም የኢየሱስ ክርስቶስ እናት የማርያም ዕጮኛ ነበር።

17እንግዲህ ከአብርሃም እስከ ዳዊት ዐሥራ አራት ትውልድ፣ ከዳዊት እስከ ባቢሎን ምርኮ ዐሥራ አራት ትውልድ፣ ከባቢሎን ምርኮ እስከ ክርስቶስ1፥17 ወይም መሲሕ “ክርስቶስ” (በግሪክ) እና “መሲሕ” (በዕብራይስጥ) ሁለቱም “የተቀባው” የሚል ትርጕም አላቸው። ልደት ዐሥራ አራት ትውልድ ይሆናል።

የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት

18የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት ታሪክ እንዲህ ነው፤ እናቱ ማርያም ለዮሴፍ ታጭታ ሳይገናኙ፣ በመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች። 19ዕጮኛዋ ዮሴፍ ጻድቅ ሰው ስለ ነበርና ማርያምን በሰው ፊት ሊያጋልጣት ስላልፈለገ በስውር ሊተዋት ወሰነ።

20በዚህ ሐሳብ ሳለ፣ የጌታ መልአክ በሕልም ተገለጠለት፤ እንዲህም አለው፤ “የዳዊት ልጅ ዮሴፍ ሆይ፤ ዕጮኛህን ማርያምን ወደ ቤትህ ለመውሰድ አትፍራ፤ የፀነሰችው በመንፈስ ቅዱስ ነውና። 21ወንድ ልጅ ትወልዳለች፤ ስሙንም ኢየሱስ1፥21 ኢየሱስ በግሪኩ ሲሆን በዕብራይስጡ ኢያሱ ነው፤ ትርጕሙም እግዚአብሔር ያድናል ማለት ነው ብለህ ትጠራዋለህ፤ ሕዝቡን ከኀጢአታቸው ያድናቸዋልና።”

22ጌታ በነቢዩ እንዲህ ሲል የተናገረው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆነ፤ 23“እነሆ፤ ድንግል ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፤ ስሙንም ዐማኑኤል ይሉታል፤” ትርጕሙም፣ “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር” ማለት ነው።

24ዮሴፍም ከእንቅልፉ ነቃ፤ ከዚያም የጌታ መልአክ እንዳዘዘው ማርያምን ወደ ቤቱ ወሰዳት።1፥24 ወደ ቤቱ ወሰዳት የሚለው የግሪኩ ቃል ሚስቱ እንድትሆን ወሰዳት ይለዋል። 25ይሁን እንጂ የበኵር ልጇን እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም፤ የተወለደውንም ሕፃን፣ “ኢየሱስ” ብሎ ጠራው።

Het Boek

Mattheüs 1:1-25

De afkomst van Jezus

1Stamboom van Jezus Christus, een afstammeling van David, die een afstammeling van Abraham was. 2Abraham was de vader van Isaak, Isaak de vader van Jakob, Jakob de vader van Juda en zijn broers,

3Juda was de vader van Peres en Zerah, Tamar was hun moeder. Peres was de vader van Chesron, Chesron de vader van Aram, 4Aram was de vader van Amminadab, Amminadab de vader van Nachson, Nachson was de vader van Salmon, 5Salmon de vader van Boaz, Rachab was zijn moeder. Boaz was de vader van Obed, Ruth was zijn moeder. Obed was de vader van Isaï 6en Isaï de vader van David, de koning. David was de vader van Salomo, Salomoʼs moeder was de vrouw van Uria. 7Salomo was de vader van Rechabeam, Rechabeam de vader van Abia. Abia was de vader van Asaf, 8Asaf de vader van Josafat, Josafat de vader van Joram, Joram was de vader van Uzzia, 9Uzzia de vader van Jotam, Jotam de vader van Achaz, Achaz de vader van Hizkia, 10Hizkia was de vader van Manasse, Manasse de vader van Amos, Amos de vader van Josia, 11Josia was de vader van Jechonja en zijn broers, die geboren werden in de tijd van de verbanning naar Babel.

12Na die verbanning werd Jechonja vader van een zoon, die Sealtiël heette. Sealtiël was de vader van Zerubbabel, 13Zerubbabel de vader van Abiud, Abiud was de vader van Eljakim, Eljakim de vader van Azor, 14Azor de vader van Sadok, Sadok de vader van Achim, Achim de vader van Eliud, 15Eliud was de vader van Eleazar, Eleazar de vader van Mattan, Mattan was de vader van Jakob, 16Jakob de vader van Jozef, die getrouwd was met Maria, de moeder van Jezus, die Christus genoemd wordt.

17Van Abraham tot David zijn dus veertien generaties, van David tot de verbanning naar Babel ook veertien generaties en van de verbanning tot de geboorte van Christus nog eens veertien generaties.

De ouders van Jezus

18De geboorte van Jezus Christus gebeurde als volgt. Toen zijn moeder Maria aan Jozef uitgehuwelijkt was maar nog niet met hem samenwoonde, bleek zij in verwachting te zijn door de Heilige Geest. 19Omdat Jozef een rechtschapen mens was en haar de schande wilde besparen, besloot hij om in stilte van haar te scheiden.

20Terwijl hij hierover lag na te denken, verscheen hem een engel van de Here in een droom. ‘Jozef, zoon van David,’ zei de engel, ‘u kunt gerust uw vrouw Maria bij u in huis nemen. Zij is in verwachting door de Heilige Geest.

21Zij zal een zoon krijgen, die u Jezus moet noemen. Dat betekent “God redt”. Want Hij zal zijn volk redden van de zonden.’ 22Daardoor zal in vervulling gaan wat God door de profeet Jesaja heeft gezegd: 23‘De maagd zal zwanger worden en een zoon baren! En men zal het kind Immanuël noemen, dat betekent: “God is met ons.” ’

24Daarna werd Jozef wakker. Hij deed wat de engel had gezegd en nam zijn vrouw bij zich in huis. 25Maar hij had geen gemeenschap met haar tot na de geboorte van het kind. En Jozef noemde Hem Jezus.