ማርቆስ 2 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 2:1-28

ኢየሱስ ሽባ ፈወሰ

2፥3-12 ተጓ ምብ – ማቴ 9፥2-8ሉቃ 5፥18-26

1ኢየሱስ ከጥቂት ቀን በኋላ ወደ ቅፍርናሆም እንደ ተመለሰ፣ ወደ ቤት መግባቱን ሕዝቡ ሰማ። 2ስለዚህ ከበሩ ውጭ እንኳ ሳይቀር ስፍራ እስኪታጣ ድረስ ብዙ ሕዝብ ተሰበሰበ፤ እርሱም የእግዚአብሔርን ቃል ሰበከላቸው። 3ጥቂት ሰዎችም አንድ ሽባ በአራት ሰዎች አሸክመው ወደ እርሱ አመጡ። 4ከሕዝቡ ብዛት የተነሣ ኢየሱስ ወዳለበት መቅረብ ስላልቻሉ፣ የቤቱን ጣራ እርሱ ባለበት በኩል ነድለው ቀዳዳ በማበጀት ሽባው የተኛበትን ዐልጋ በዚያ አወረዱ። 5ኢየሱስም እምነታቸውን አይቶ ሽባውን፣ “አንተ ልጅ፣ ኀጢአትህ ተሰርዮልሃል!” አለው።

6በዚያ ተቀምጠው የነበሩ አንዳንድ ጸሐፍት ስለዚህ ነገር በልባቸው እያሰላሰሉ፣ 7“ይህ ሰው እንዴት እንዲህ ይላል? በአምላክ ላይ የስድብ ቃል እየተናገረ እኮ ነው! ከአንዱ ከእግዚአብሔር በስተቀር ማን ኀጢአትን ሊያሰተሰርይ ይችላል?” ብለው አሰቡ።

8ኢየሱስም ወዲያው በልባቸው የሚያስቡትን በመንፈሱ ተረድቶ፣ “እንዴት እንዲህ ታስባላችሁ? 9ሽባውን፣ ‘ኀጢአትህ ተሰርዮልሃል’ ከማለትና፣ ‘ተነሥተህ ዐልጋህን ተሸክመህ ሂድ’ ከማለት የቱ ይቀልላል? 10ነገር ግን የሰው ልጅ በምድር ላይ ኀጢአትን ለማስተስረይ ሥልጣን እንዳለው እንድታውቁ” በማለት ሽባውን፣ 11“ተነሥተህ ዐልጋህን ተሸክመህ ወደ ቤትህ ሂድ” አለው። 12እርሱም ተነሥቶ ሁሉም እያዩት ዐልጋውን ተሸክሞ ሄደ፤ በስፍራው የነበሩትም ሁሉ በሁኔታው በመደነቅ፣ “የዚህ ዐይነት ነገር ፈጽሞ አይተን አናውቅም!” በማለት ለእግዚአብሔር ምስጋና አቀረቡ።

የሌዊ መጠራት

2፥14-17 ተጓ ምብ – ማቴ 9፥9-13ሉቃ 5፥27-32

13ኢየሱስም ዳግም ወደ ባሕሩ ዳርቻ ወጣ፤ ሕዝቡም በብዛት ወደ እርሱ መጡ፤ እርሱም አስተማራቸው። 14በዚያም ሲያልፍ የእልፍዮስን ልጅ ሌዊን በቀረጥ መቀበያው ስፍራ ተቀምጦ አየውና፣ “ተከተለኝ” አለው፤ እርሱም ተነሥቶ ተከተለው።

15በማቴዎስ ቤት በማእድ ተቀምጦ ሳለ፣ ብዙ ቀረጥ ሰብሳቢዎችና ኀጢአተኞች ተከትለውት ስለ ነበር፣ ከኢየሱስና ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ይመገቡ ነበር። 16ከፈሪሳውያን ወገን የነበሩ ጸሐፍት ከኀጢአተኞችና ከቀረጥ ሰብሳቢዎች ጋር ሲበላ ባዩት ጊዜ፣ ደቀ መዛሙርቱን “ከቀረጥ ሰብሳቢዎችና ከኀጢአተኞች ጋር ለምን ይበላል?” ሲሉ ጠየቋቸው።

17ኢየሱስም የሚናገሩትን ሰምቶ፣ “ሐኪም የሚያስፈልጋቸው ሕመምተኞች እንጂ ጤነኞች አይደሉም፤ እኔ ኀጢአተኞችን እንጂ ጻድቃንን ወደ ንስሓ ልጠራ አልመጣሁም” አላቸው።

ስለ ጾም የቀረበ ጥያቄ

2፥18-22 ተጓ ምብ – ማቴ 9፥14-17ሉቃ 5፥33-38

18የዮሐንስ ደቀ መዛሙርትና ፈሪሳውያን ይጾሙ ነበር፤ አንዳንድ ሰዎችም መጥተው ኢየሱስን፣ “የዮሐንስና የፈሪሳውያን ደቀ መዛሙርት ሲጾሙ፣ የአንተ ደቀ መዛሙርት የማይጾሙት ለምንድን ነው?” አሉት።

19ኢየሱስም፣ እንዲህ አላቸው፤ “ሙሽራው ከእነርሱ ጋር እያለ ሚዜዎቹ ሊጾሙ ይችላሉን? ሙሽራው ከእነርሱ ጋር እያለ ሊጾሙ አይችሉም፤ 20ሙሽራው ከእነርሱ የሚወሰድበት ወቅት ይመጣል፤ በዚያን ጊዜ ግን ይጾማሉ።

21“በአሮጌ ልብስ ላይ አዲስ ጨርቅ የሚጥፍ ማንም የለም፤ ይህ ቢደረግ ግን፣ አዲሱ ጨርቅ አሮጌውን ይቦጭቀዋል፤ ቀዳዳውም የባሰ ይሰፋል። 22እንዲሁም አዲስ የወይን ጠጅ በአሮጌ አቍማዳ የሚያስቀምጥ የለም፤ ይህ ከተደረገማ የወይን ጠጁ አቍማዳውን ያፈነዳዋል፤ የወይን ጠጁም አቍማዳውም ይበላሻሉ። ስለዚህ አዲስ የወይን ጠጅ መቀመጥ ያለበት በአዲስ አቍማዳ ነው።”

ኢየሱስ የሰንበት ጌታ ነው

2፥23-28 ተጓ ምብ – ማቴ 12፥1-8ሉቃ 6፥1-5

3፥1-6 ተጓ ምብ – ማቴ 12፥9-14ሉቃ 6፥6-11

23በሰንበት ቀን ኢየሱስ በዕርሻ መካከል ሲያልፍ፣ አብረውት በመጓዝ ላይ የነበሩት ደቀ መዛሙርቱ እሸት ይቀጥፉ ጀመር። 24ፈሪሳውያንም፣ “እነሆ፤ በሰንበት ቀን ለምን የተከለከለ ነገር ያደርጋሉ?” ሲሉ ጠየቁት።

25እርሱም እንዲህ አላቸው፤ “ዳዊት በተራበና የምግብ ፍላጎት በጸናበት ጊዜ አብረውት ከነበሩት ሰዎች ጋር ያደረገውን አላነበባችሁምን? 26በሊቀ ካህናቱ በአብያታር ዘመን ወደ እግዚአብሔር ቤት ገብቶ፣ ካህናት ብቻ እንዲበሉት የተፈቀደውን የተቀደሰ ኅብስት ራሱ በልቶ አብረውት ለነበሩትም ሰዎች ሰጣቸው።”

27ደግሞም እንዲህ አላቸው፤ “ሰንበት ለሰው ተፈጠረ እንጂ፣ ሰው ለሰንበት አልተፈጠረም፤ 28ስለዚህ የሰው ልጅ የሰንበት ጌታዋ ነው።”

Habrit Hakhadasha/Haderekh

הבשורה על-פי מרקוס 2:1-28

1כעבור ימים אחדים חזר ישוע לכפר־נחום, ומיד נפוצו שמועות על בואו בכל העיר. 2הבית שבו התארח התמלא במהרה עד אפס מקום. אפילו החצר הייתה מלאה אנשים, עד שלא היה מקום לאף אדם נוסף, וישוע לימד אותם את כתבי־הקודש.

3בין הקהל בחצר היו ארבעה אנשים שנשאו אדם משותק על אלונקה. 4בגלל הקהל הרב הם לא יכלו להיכנס לתוך הבית ולדבר עם ישוע. לכן הם טיפסו על הגג, הזיזו רעפים אחדים ממקומם והורידו את האלונקה אל אמצע החדר, אל המקום שבו עמד ישוע.

5כשראה ישוע את אמונתם, פנה אל האיש המשותק ואמר: ”בני, נסלחו לך חטאיך!“

6היו כמה מורי הלכה שנכחו במקום, ואלה אמרו בלבם: 7”מה הוא מגדף? למי הוא חושב את עצמו, לאלוהים? הרי רק אלוהים יכול לסלוח על חטאים!“ 8ישוע ידע את מחשבותיהם ולכן שאל: ”מדוע דברי מטרידים אתכם? 9‏-10לי, המשיח, יש סמכות לסלוח חטאים עלי־אדמות. אני אוכיח לכם שאני לא רק מדבר, אלא גם עושה – מיד תראו כיצד אני מרפא את האיש הזה.“ 11הוא פנה אל האיש המשותק ופקד עליו: ”קום! קפל את האלונקה שלך ולך לביתך, כי נרפאת!“

12האיש קפץ על רגליו, קיפל את האלונקה ופילס לו דרך בתוך הקהל הנדהם. כולם היללו את אלוהים מעומק לבם וקראו בפליאה: ”אף פעם לא ראינו דבר כזה!“

13ישוע יצא שוב לחוף הים. אנשים רבים התאספו סביבו והוא לימד אותם. 14כאשר התהלך על החוף פגש את לוי, בנו של חלפי, יושב בבית־המכס. ”בוא אתי,“ הזמינו ישוע, ”בוא והיה תלמיד שלי.“ לוי עזב את בית־המכס והלך עם ישוע.

15באותו ערב הזמין לוי לארוחה בביתו את גובי־המכס מהעבודה ואנשים רגילים מהרחוב, כדי שתהיה להם הזדמנות לפגוש את ישוע ותלמידיו (אנשים רבים רצו לפגוש את ישוע פנים אל פנים ולדבר איתו). 16אחדים מהסופרים והפרושים ראו את ישוע אוכל בחברת אנשים בעלי שם רע. ”כיצד הוא יכול לאכול עם האנשים האלה?“ שאלו את תלמידיו.

17ישוע שמע את שאלתם והשיב: ”החולים זקוקים לרופא ולא הבריאים. לא באתי לקרוא לצדיקים לחזור בתשובה, כי אם לחוטאים.“

18תלמידי יוחנן ותלמידי הפרושים נהגו לצום, כנהוג במסורת היהודית. יום אחד באו מספר אנשים אל ישוע ושאלו אותו מדוע תלמידיו אינם צמים כמו כולם.

19השיב להם ישוע: ”האם ייתכן שידידי החתן יסרבו לאכול במסיבת חתונתו? האם ייתכן שיתאבלו בזמן שהחתן נמצא אתם? 20אולם יבוא יום שהחתן יילקח מהם, ואז הם יצומו. 21למה הדבר הזה דומה? לאדם התופר טלאי מבד חדש על בגד ישן ובלה; מה יקרה? הטלאי מהבד החדש יינתק ויגדיל את החור בבגד. 22הדבר דומה גם לאדם הממלא יין חדש בתוך חביות רקובות. הרי היין יבקע את החביות ויישפך החוצה. יין חדש יש לשמור בחביות חדשות.“

23באחת השבתות הלכו ישוע ותלמידיו דרך שדה תבואה, והתלמידים קטפו שיבולים ואכלו את הגרעינים.

24”ראה מה הם עושים!“ התנפלו הפרושים על ישוע. ”מדוע הם קוטפים שיבולים בשבת? הלא הם עוברים על חוקי התורה ומחללים את השבת!“

25‏-26”האם מעולם לא קראתם מה עשה דוד המלך?“ השיב להם ישוע. ”כאשר דוד המלך ואנשיו היו רעבים הם נכנסו לאוהל מועד – בימי אביתר הכוהן – ואכלו את לחם הפנים שהיה מיועד לכוהנים בלבד. הלא גם זה היה בניגוד לחוקי התורה. 27דעו לכם כי השבת ניתנה למען בני־האדם, ולא בני־האדם למען השבת. 28ובן האדם הוא אדון השבת.“