ማሕልየ መሓልይ 3 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

ማሕልየ መሓልይ 3:1-11

1ሌሊቱን ሙሉ በዐልጋዬ ላይ ሆኜ፣

ውዴን ተመኘሁ፤

ተመኘሁት፤ ነገር ግን አላገኘሁትም።

2ተነሥቼ ወደ ከተማዪቱ እወጣለሁ፤

በዋና ዋና መንገዶችና በአደባባዮች እዘዋወራለሁ፤

ውዴንም እፈልገዋለሁ፤

ስለዚህም ፈለግሁት፤ ነገር ግን አላገኘሁትም።

3በከተማዪቱ ውስጥ ሲዘዋወሩ፣

የከተማዪቱ ጠባቂዎች አገኙኝ፤

እኔም፣ “ውዴን አይታችኋል?”

አልኋቸው።

4ከእነርሱ ጥቂት ዕልፍ እንዳልሁ፣

ውዴን አገኘሁት፤ ያዝሁት፤

ወደ እናቴ ቤት እስካመጣው፣

በማሕፀን ወደ ተሸከመችኝም ዕልፍኝ

እስካገባው ድረስ አልለቀውም።

5እናንት የኢየሩሳሌም ቈነጃጅት፤

ራሱ እስኪፈልግ ድረስ፣

ፍቅርን እንዳታስነሡት ወይም እንዳትቀሰቅሱት፣

በሚዳቋና በሜዳ ዋሊያ አማጥናችኋለሁ።

6ከከርቤና ከዕጣን፣

ከነጋዴም ቅመማ ቅመም ሁሉ በተዘጋጀ ሽቱ፣

መዐዛዋ የሚያውድ፣

እንደ ጢስ ዐምድ ከምድረ በዳ የምትወጣው ይህች ማን ናት?

7እነሆ፤ የሰሎሞን ሠረገላ

በታዋቂዎቹ የእስራኤል መኳንንት፣

ስድሳ ጦረኞች ታጅባለች፤

8ሁሉም ሰይፍ የታጠቁ፣

ሁሉም በጦርነት የተፈተኑ ናቸው፤

የሌሊት አደጋን ለመከላከልም፣

እያንዳንዳቸው ሰይፋቸውን በወገባቸው ታጥቀዋል።

9ንጉሥ ሰሎሞን የራሱን ሠረገላ ሠራ፤

የሠራውም ከሊባኖስ በመጣ ዕንጨት ነው።

10ምሰሶዎቹን ከብር፣

መደገፊያውንም ከወርቅ ሠራ፤

መቀመጫውም በሐምራዊ ሐር የተሸፈነ ነው፤

ውስጡም በኢየሩሳሌም ቈነጃጅት፣

አምሮ የተለበጠ ነው።3፥10 ወይም የተለበጠውም ውስጥ፣ ከኢየሩሳሌም ቈነጃጅት የሆነ የፍቅር ስጦታ

11እናንት የጽዮን ቈነጃጅት ውጡ፤

ንጉሥ ሰሎሞን አክሊሉን ደፍቶ እዩት፤

ዘውዱም ልቡ ሐሤት ባደረገባት፣

በዚያች በሰርጉ ዕለት፣

እናቱ የደፋችለት ነው።

King James Version

Song of Solomon 3:1-11

1By night on my bed I sought him whom my soul loveth: I sought him, but I found him not. 2I will rise now, and go about the city in the streets, and in the broad ways I will seek him whom my soul loveth: I sought him, but I found him not. 3The watchmen that go about the city found me: to whom I said, Saw ye him whom my soul loveth? 4It was but a little that I passed from them, but I found him whom my soul loveth: I held him, and would not let him go, until I had brought him into my mother’s house, and into the chamber of her that conceived me. 5I charge you, O ye daughters of Jerusalem, by the roes, and by the hinds of the field, that ye stir not up, nor awake my love, till he please.

6¶ Who is this that cometh out of the wilderness like pillars of smoke, perfumed with myrrh and frankincense, with all powders of the merchant?

7Behold his bed, which is Solomon’s; threescore valiant men are about it, of the valiant of Israel. 8They all hold swords, being expert in war: every man hath his sword upon his thigh because of fear in the night. 9King Solomon made himself a chariot of the wood of Lebanon.3.9 a chariot: or, a bed 10He made the pillars thereof of silver, the bottom thereof of gold, the covering of it of purple, the midst thereof being paved with love, for the daughters of Jerusalem. 11Go forth, O ye daughters of Zion, and behold king Solomon with the crown wherewith his mother crowned him in the day of his espousals, and in the day of the gladness of his heart.