ሚክያስ 2 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ሚክያስ 2:1-13

የእግዚአብሔርና የሰው ዕቅድ

1ክፉ ለመሥራት ለሚያቅዱ፣

በመኝታቸው ሳሉ ተንኰል ለሚያውጠነጥኑ ወዮላቸው!

ሲነጋ በማለዳ ይፈጽሙታል፤

የሚያደርጉበት ኀይል በእጃቸው ነውና።

2ዕርሻ ይመኛሉ፤ ይይዙታልም፤

ቤት ይመኛሉ፤ ይወስዱታልም፤

የሰውን ቤት፣

የባልንጀራን ርስት አታልለው ይወስዳሉ።

3ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“እነሆ፤ በዚያ ሕዝብ ላይ ጥፋት ላመጣ ዐቅጃለሁ፤

ከዚህም ለማምለጥ አትችሉም።

ከእንግዲህ በትዕቢት አትመላለሱም፤

የመከራ ጊዜ ይሆናልና።

4በዚያ ቀን ሰዎች ይሣለቁባችኋል፤

በሐዘን እንጕርጕሮ እንዲህ እያሉ ያፌዙባችኋል፤

‘እኛ ፈጽሞ ጠፍተናል፤

የወገኔ ርስት ተከፋፍሏል።

ከእኔ ነጥቆ ወስዶ፣

ዕርሻዎቻችንን ላሸነፉን አከፋፈለ።’ ”

5ስለዚህ በእግዚአብሔር ጉባኤ ውስጥ፣

መሬት በዕጣ የሚያካፍል ማንም አይኖርም።

ሐሰተኞች ነቢያት

6ነቢያቶቻቸው፣ “ትንቢት አትናገርብን፤

ስለ እነዚህ ነገሮች ትንቢት አትናገር፤

ውርደት አይደርስብንም” ይላሉ።

7የያዕቆብ ቤት ሆይ፤ እንዲህ ሊባል ይገባልን?

የእግዚአብሔር መንፈስ የማይታገሥ ነውን?

እንዲህ ያሉ ነገሮችንስ ያደርጋልን?”

“መንገዱ ቀና ለሆነ፣

ቃሌ መልካም አያደርግምን?

8በመጨረሻ በሕዝቤ ላይ ጠላት ሆናችሁ

ተነሣችሁ፤

የጦርነት ሐሳብ ሳይኖራቸው፣

በሰላም ከሚያልፉ ሰዎች ላይ

ማለፊያ መጐናጸፊያ ገፈፋችሁ።

9ከሚወድዱት ቤታቸው፣

የሕዝቤን ሴቶች አስወጣችኋቸው፤

ክብሬን ከልጆቻቸው

ለዘላለም ወሰዳችሁ።

10ተነሡና ከዚያ ሂዱ፤

ይህ ማረፊያ ቦታችሁ አይደለምና፤

ምክንያቱም ረክሷል፤

ክፉኛም ተበላሽቷል።

11ሐሰተኛና አታላይ ሰው መጥቶ፣

‘ስለ ብዙ የወይን ጠጅና ስለሚያሰክር መጠጥ ትንቢት እነግራችኋለሁ’ ቢል፣

ለዚህ ሕዝብ ተቀባይነት ያለው ነቢይ ይሆናል።

የትድግና ተስፋ

12“ያዕቆብ ሆይ፤ በርግጥ ሁላችሁንም እሰበስባለሁ፤

የእስራኤልንም ትሩፍ በአንድነት አመጣለሁ፤

በጕረኖ ውስጥ እንዳሉ በጎች በመሰማሪያ ላይ እንዳለ መንጋ በአንድነት

እሰበስባቸዋለሁ፤

ቦታውም በሕዝብ ይሞላል።

13የሚሰብረው ወጥቶ በፊታቸው ይሄዳል፤

እነርሱም በሩን በመስበር ወጥተው ይሄዳሉ።

እግዚአብሔር እየመራቸው፣

ንጉሣቸው ቀድሟቸው ይሄዳል።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

彌迦書 2:1-13

欺壓者的命運

1躺在床上圖謀不軌、

盤算作惡的人有禍了!

天一亮,他們就依仗手中的權勢行惡。

2他們貪圖田地,就去霸佔;

想要房屋,就去搶奪。

他們欺壓人,

詐取別人的家園和產業。

3所以,耶和華說:

「我正計劃降災懲罰你們,

你們無法逃脫,

再也不能趾高氣揚,

因為這是你們災禍臨頭的日子。

4到那日,

人們要唱哀歌譏諷你們說,

『我們徹底完了,

耶和華把我們的產業轉給別人。

祂竟拿走我們的產業,

把田地分給擄掠我們的人。』」

5因此,他們在耶和華的會眾中將無人抽籤分地。

6他們的先知說:

「不要說預言了,

不要預言這種事,

我們不會蒙受羞辱。」

7雅各家啊,你們怎能說:

「耶和華已經不耐煩了嗎?

祂會做這些事嗎?」

「我的話豈不有益於行為正直的人嗎?

8近來,你們像仇敵一樣起來攻擊我的子民2·8 你們像仇敵一樣起來攻擊我的子民」或譯「我的子民如仇敵一樣興起來」。

你們剝去那些如從戰場歸來一樣毫無戒備的過路人的外衣。

9你們把我子民中的婦女從她們的幸福家園趕走,

又從她們的子女身上永遠地奪去我的尊榮。

10你們起來走吧!

這裡不再是你們的安居之地!

因為這裡已遭玷污,

被徹底毀壞。

11倘若有騙子撒謊說,

『我預言你們會有美酒佳釀。』

他就會成為這個民族的先知。

12雅各家啊,

我必把你們都聚集起來,

我必把以色列的餘民集合起來。

我要將他們安頓在一起,

好像羊圈裡的羊,

又如草場上的羊群;

那裡必人聲鼎沸。

13開路者要走在他們前面,

帶領他們衝出敵人的城門。

他們的王走在前面,

耶和華親自引導他們。」