ሚክያስ 1 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ሚክያስ 1:1-16

1በይሁዳ ነገሥታት በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን ወደ ሞሬታዊው ወደ ሚክያስ የመጣው የእግዚአብሔር ቃል፣ ስለ ሰማርያና ስለ ኢየሩሳሌም ያየው ራእይ ይህ ነው፤

2እናንተ አሕዛብ ሆይ፤ ሁላችሁም ስሙ፤

ምድር ሆይ፤ በውስጧም የምትኖሩ ሁሉ አድምጡ፤

ጌታ ከቅዱስ መቅደሱ፣

ልዑል እግዚአብሔር በእናንተ ላይ ይመሰክርባችኋል።

በሰማርያና በኢየሩሳሌም ላይ የተላለፈ ፍርድ

3እነሆ፤ እግዚአብሔር ከመኖሪያ ስፍራው ይመጣል፤

ወርዶም በምድር ከፍታዎች ላይ ይራመዳል።

4ተራሮች ከሥሩ ይቀልጣሉ፤

ሸለቆዎችም ይሰነጠቃሉ፤

በእሳት ፊት እንዳለ ሰም፣

በገደል ላይ እንደሚወርድ ፈሳሽ ይሆናሉ።

5ይህ ሁሉ የሚሆነው ስለ ያዕቆብ በደል፣

ስለ እስራኤልም ቤት ኀጢአት ነው።

የያዕቆብ በደል ምንድን ነው?

ሰማርያ አይደለችምን?

የይሁዳስ የኰረብታ መስገጃ ምንድን ነው?

ኢየሩሳሌም አይደለችምን?

6“ስለዚህ ሰማርያን የፍርስራሽ ክምር፣

ወይን የሚተከልባትም ስፍራ አደርጋታለሁ፤

ድንጋዮቿን ወደ ሸለቆ አወርዳለሁ፤

መሠረቷንም ባዶ አደርጋለሁ።

7ጣዖቶቿ ሁሉ ይሰባበራሉ፤

ለቤተ መቅደሷ የቀረበው ገጸ በረከት በእሳት ይቃጠላል፤

ምስሎቿን ሁሉ እደመስሳለሁ፤

ገጸ በረከቷን በዝሙት ዐዳሪነት እንደ ሰበሰበች ሁሉ፣

አሁንም ገጸ በረከቷ የዝሙት ዐዳሪነት ዋጋ መቀበያ ይሆናል።”

ልቅሶና ሐዘን

8በዚህ ምክንያት አለቅሳለሁ፤ ዋይ ዋይም እላለሁ፤

ባዶ እግሬንና ዕርቃኔን እሄዳለሁ፤

እንደ ቀበሮ አላዝናለሁ፤

እንደ ጕጕትም አቃስታለሁ።

9ቍስሏ የማይሽር ነውና፤

ለይሁዳ ተርፏል፤

እስከ ሕዝቤ መግቢያ በር፣

እስከ ኢየሩሳሌም እንኳ ደርሷል።

10በጌት1፥10 ጌት የሚለው ቃል በዕብራይስጡ አውራ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። አታውሩት፤

ከቶም አታልቅሱ1፥10 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ሲስማማ፣ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን በአኮ ላይ አታልቅሱ ይላል። በአኮ የሚለው የዕብራይስጡ ቃል አለቀሰ ከሚለው የዕብራይስጡ ቃል ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው።

በቤትዓፍራ1፥10 ቤትዓፍራ ትርጕሙ የትቢያ ቤት ማለት ነው።

በትቢያ ላይ ተንከባለሉ።

11እናንት በሻፊር1፥11 ሻፊር ትርጕሙ አስደሳች ማለት ነው። የምትኖሩ፣

ዕርቃናችሁን ሆናችሁ በኀፍረት ዕለፉ፤

በጸዓናን1፥11 ጸዓናን የሚለው ቃል በዕብራይስጡ ውጣ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የሚኖሩ

ከዚያ አይወጡም፤

ቤትዔጼል በሐዘን ላይ ናት፤

ለእናንተም መጠጊያ ልትሆን አትችልም።

12ከመከራው መገላገልን በመሻት፣

በማሮት1፥12 ማሮት የሚለው ቃል በዕብራይስጡ መራራ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የሚኖሩ በሥቃይ

ይወራጫሉ፤

እስከ ኢየሩሳሌም በር ሳይቀር፣

ክፉ ነገር ከእግዚአብሔር ዘንድ መጥቷልና።

13እናንት በለኪሶ1፥13 ለኪሶ የሚለው ቃል በዕብራይስጡ ቡድን ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የምትኖሩ፣

ፈረሶችን ከሠረገላው ጋር አያይዙ፤

ለጽዮን ሴት ልጅ፣

የኀጢአት መጀመሪያ እናንት ነበራችሁ፤

የእስራኤል በደል

በእናንተ ዘንድ ተገኝቷልና።

14ስለዚህ እናንተ ለሞሬሼትጌት፣

ማጫ ትሰጣላችሁ፤

የአክዚብ1፥14 አክዚብ ትርጕሙ አታላይ ወይም ማታለል ማለት ነው። ከተማ፣

ለእስራኤል ነገሥታት መታለያ ትሆናለች።

15እናንት በመሪሳ1፥15 መሪሳ የሚለው ቃል በዕብራይስጡ ድል አድራጊ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ አነባበብ አለው። የምትኖሩ

ድል አድራጊ አመጣባችኋለሁ፤

ያ የእስራኤል ክብር የሆነው

ወደ ዓዶላም ይመጣል።

16ደስ ለምትሰኙባቸው ልጆቻችሁ፣

በሐዘን ራሳችሁን ተላጩ፤

ራሳችሁን እንደ አሞራ ራስ ተመለጡት፤

ከእናንተ በምርኮ ይወሰዳሉና።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

彌迦書 1:1-16

1猶大約坦亞哈斯希西迦執政期間,耶和華把祂的話傳給了摩利沙彌迦。他看到了有關撒瑪利亞耶路撒冷的異象。

審判將臨

2萬民啊,

你們都要聽!

大地和地上的萬物啊,

你們要側耳傾聽!

主耶和華從祂的聖殿裡作證指控你們。

3看啊,耶和華離開祂的居所,

從天降臨,

腳踏大地的高處。

4群山在祂腳下熔化,

猶如火中的蠟;

山谷崩裂,

岩石如水沿山坡傾瀉。

5這一切都是因為雅各的叛逆,

以色列家的罪惡。

雅各的叛逆在哪裡呢?

豈不是在撒瑪利亞嗎?

猶大的邱壇在哪裡呢?

豈不是在耶路撒冷嗎?

6「所以,我耶和華要使撒瑪利亞淪為荒野的廢墟,

成為種葡萄的地方。

我要把她的石頭拋進山谷,

直到露出她的根基。

7她所有的神像都要被打碎,

她所得的淫資都要化為灰燼;

我要毀滅她的一切偶像。

她以淫資得來的偶像,

也要被用作妓女的淫資。」

先知的哀傷

8為此,我要痛哭哀號,

我要赤身光腳而行,

像豺狼哀嚎,

如鴕鳥悲鳴。

9因為撒瑪利亞的創傷無法救治,

已經禍及猶大

直逼我百姓的城門,直逼耶路撒冷

10不要在迦特宣揚,

也不要哭泣,

要在伯·亞弗拉的灰塵中打滾。

11沙斐的居民啊,

你們將赤身露體,

被羞辱地擄去。

撒南的居民不敢出城,

伯·以薛在痛哭,

你們已失去它的庇護。

12瑪律的居民痛苦不堪,

渴望得到拯救,

因為耶和華已把災難降到耶路撒冷的城門。

13拉吉的居民啊,

用駿馬套車逃命吧!

是你們首先唆使錫安城犯罪,

在你們身上看到了以色列的罪惡。

14去向摩利設·迦特贈送告別禮物吧!

亞革悉人必令以色列諸王受騙上當。

15瑪利沙的居民啊,

我要使征服者到你們那裡。

以色列的領袖1·15 以色列的領袖」希伯來文是「以色列的榮耀」。要躲到亞杜蘭

16猶大人啊,你們要剃光頭髮,

為你們所愛的兒女悲傷;

要剃得如禿鷹一樣光禿,

因為他們要被擄到遠方。