መዝሙር 63 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 63:1-11

መዝሙር 63

እግዚአብሔርን መፈለግ

በይሁዳ ምድረ በዳ በነበረ ጊዜ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ አምላኬ ነህ፤

አንተን ከልብ እሻለሁ፤ ውሃ በሌለበት፣

በደረቅና በተራቈተ ምድር፣

ነፍሴ አንተን ተጠማች፤

ሥጋዬም አንተን ናፈቀች።

2ስለዚህ በመቅደስ ውስጥ አየሁህ፤

ኀይልህንና ክብርህንም ተመለከትሁ።

3ምሕረትህ ከሕይወት ይበልጣልና፤

ከንፈሮቼ ያመሰግኑሃል።

4እንግዲህ፣ በሕይወቴ ዘመን አመሰግንሃለሁ፤

በአንተም ስም እጆቼን አነሣለሁ።

5ነፍሴ በቅቤና በሥብ እንደሚረካ ሰው ትረካለች፤

አፌም በሚያዜሙ ከንፈሮች በደስታ ያወድስሃል።

6በመኝታዬ ዐስብሃለሁ፤

ሌሊቱንም ሁሉ ስለ አንተ አሰላስላለሁ።

7አንተ ረዳቴ ነህና፣

በክንፎችህ ሥር ተጠልዬ በደስታ እዘምራለሁ።

8ነፍሴ አንተን የሙጥኝ ብላለች፤

ቀኝ እጅህም ደግፋ ይዛኛለች።

9ነፍሴን ለማጥፋት የሚሹ ግን፣

ወደ ምድር ጥልቅ ይወርዳሉ፤

10ለሰይፍ ዐልፈው ይሰጣሉ፤

የቀበሮዎችም ምግብ ይሆናሉ።

11ንጉሥ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለዋል፤

በእግዚአብሔርም ስም ቃል የሚገቡ ሁሉ ይከብራሉ፤

የሐሰተኞች አንደበትም ትዘጋለች።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 63:1-11

第 63 篇

渴慕上帝

大衛在曠野時作的詩。

1上帝啊,你是我的上帝,

我迫切地尋求你!

在乾旱荒涼之地,

我的心渴慕你,渴慕你!

2我曾在你的聖所瞻仰你的榮面,

目睹你的權能和榮耀。

3你的慈愛比生命更寶貴,

我的嘴唇要讚美你。

4我一生都要讚美你,

奉你的名舉手禱告。

5我心滿意足,如享盛宴,

唱起歡快的歌讚美你。

6我躺在床上的時候思念你,

整夜地思想你。

7因為你是我的幫助,

我在你翅膀的蔭庇下歡歌。

8我的心依戀你,

你的右手扶持我。

9那些圖謀毀滅我的人必下到陰間。

10他們必喪身刀下,

成為豺狼的食物。

11但王要因上帝而歡欣,

凡信靠祂的人必歡喜快樂,

說謊者的口必被封住。