መዝሙር 62 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 62:1-12

መዝሙር 62

ተስፋ በእግዚአብሔር ላይ ብቻ

ለመዘምራን አለቃ፤ ለኤዶታም፤ የዳዊት መዝሙር።

1ነፍሴ ዕረፍት የምታገኘው በእግዚአብሔር ብቻ ነው፤

ድነቴም የሚመጣልኝ ከእርሱ ዘንድ ነው።

2ዐለቴና መድኀኒቴ እርሱ ብቻ ነው፤

መጠጊያዬም እርሱ ነው፤ ከቶም አልናወጥም።

3ሰውን የምታጠቁት እስከ መቼ ነው?

ይህን የዘመመ ግድግዳ፣ የተንጋደደ ዐጥር፣

ሁላችሁ ገፍታችሁ ልትጥሉት ትሻላችሁ?

4ከታላቅ ክብሩ ሊያዋርዱት፣

ይህን አንድ ነገር ወጠኑ፤

ሐሰት ባለበት ነገር ደስ ይሰኛሉ፤

በአፋቸው ይመርቃሉ፤

በልባቸው ግን ይራገማሉ። ሴላ

5ነፍሴ ሆይ፤ ዐርፈሽ እግዚአብሔርን ብቻ ጠብቂ፤

ተስፋዬ ከእርሱ ዘንድ ነውና።

6ዐለቴና መድኀኒቴ እርሱ ብቻ ነው፤

መጠጊያዬም እርሱ ነው፤ እኔም አልናወጥም።

7መዳኔና ክብሬ በእግዚአብሔር ነው፤62፥7 ወይም ልዑል እግዚአብሔር ድነቴና ክብሬ ነው ተብሎ መተርጐም ይችላል።

ብርቱ ዐለቴና መሸሸጊያዬ በእግዚአብሔር ነው።

8ሰዎች ሆይ፤ ሁልጊዜ በእርሱ ታመኑ፤

ልባችሁን በፊቱ አፍስሱ፤

እግዚአብሔር መጠጊያችን ነውና። ሴላ

9ከተናቀ ወገን መወለድ ከንቱ፣

ከከበረውም መወለድ ሐሰት ነው።

በሚዛን ላይ ከፍ ብለው ቢታዩም፣

ሁሉም በአንድነት ከነፋስ የቀለሉ ናቸው።

10በዝርፊያ አትታመኑ፤

በቅሚያም ተስፋ አታድርጉ፤

በዚህ ብትበለጽጉም፣

ልባችሁ ይህን አለኝታ አያድርግ።

11እግዚአብሔር አንድ ነገር ተናገረ፤

እኔም ይህን ሁለት ጊዜ ሰማሁ፤

ኀይል የእግዚአብሔር ነው።

12ጌታ ሆይ፤ ምሕረትም የአንተ ነው፤

አንተ ለእያንዳንዱ፣

እንደ ሥራው ትከፍለዋለህ።

Swedish Contemporary Bible

Psaltaren 62:1-13

Psalm 62

En tröstepsalm

1För körledaren, till Jedutun62:1 Jedutun var en av Davids musiker, se 1 Krön 16:41.. En psalm av David.

2Bara hos Gud finner jag ro,

från honom kommer min räddning.

3Endast han är min klippa,

min räddning och min borg.

Jag ska aldrig vackla.

4Hur länge ska ni ansätta en människa,

kasta er över honom allesammans,

som mot en lutande vägg,

eller en mur som snart störtar samman?

5De tänker störta ner honom från hans höga plats,

och de gillar lögn.

Med sin mun välsignar de,

men i sitt inre förbannar de. Séla

6Bara hos Gud finner jag ro,

från honom kommer mitt hopp.

7Endast han är min klippa,

min räddning och min borg.

Jag ska aldrig vackla.

8Min frälsning och min ära finns hos Gud.

Han är min tillflykt, min starka klippa.

9Förtrösta alltid på honom, du folk!

utgjut ditt hjärta för honom, för Gud är vår tillflykt. Séla

10Människobarnen är bara en vindpust,

även de höga bland dem är en lögn.

I vågskålen väger de lätt,

ja, mindre än luft.

11Sätt inte er tillit till våld

eller ert hopp till stöldgods.

Om er rikedom växer,

fäst inte ert hjärta vid den.

12Ett har Gud talat, två saker har jag hört:

att Gud har styrkan,

13och att du, Herre, är nådig

och lönar var och en efter vad han gjort.