መዝሙር 6 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 6:1-10

መዝሙር 6

በጭንቅ ጊዜ የቀረበ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር በሸሚኒት6 ርእሱ በሙዚቃ ውስጥ የሚጠቀሙበት ቃል ሳይሆን አይቀርም።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ በቍጣህ

አትገሥጸኝ፤

በመዓትህም አትቅጣኝ።

2እግዚአብሔር ሆይ፤ ዐቅመ ቢስ ነኝና ማረኝ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ዐጥንቶቼ ተናግተዋልና ፈውሰኝ።

3ነፍሴ እጅግ ታውካለች፤

እስከ መቼ፣ አንተ እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህ እስከ መቼ ድረስ ይሆናል?

4እግዚአብሔር ሆይ፤ ተመለስና ሕይወቴን ታደጋት፤

ስለ ጽኑ ፍቅርህም አድነኝ፤

5በሞት የሚያስታውስህ የለምና፤

በሲኦልስ6፥5 ወይም በመቃብር ማን ያመሰግንሃል?

6ከመቃተቴ የተነሣ ዝያለሁ፤

ሌሊቱን ሁሉ በልቅሶ ዐልጋዬን አርሳለሁ፤

መኝታዬንም በእንባዬ አሾቃለሁ።

7ዐይኖቼ በሐዘን ብዛት ደክመዋል፤

ከጠላቶቼም ሁሉ የተነሣ ማየት ተስኗቸዋል።

8እናንተ ክፉ አድራጊዎች ሁሉ፤ ከእኔ ራቁ፤

እግዚአብሔር የልቅሶዬን ድምፅ ሰምቷልና።

9እግዚአብሔር ልመናዬን አድምጧል፤

እግዚአብሔር ጸሎቴን ይቀበላል።

10ጠላቶቼ ሁሉ ያፍራሉ፤ እጅግም ይደነግጣሉ፤

በመጡበት ይመለሳሉ፤ ድንገትም ይዋረዳሉ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 6:1-10

6

1主よ、お願いです。

御怒りのままに私を罰しないでください。

2ああ主よ、あわれんでください。

私は弱い者です。どうかいやしてください。

私は病んでいるのです。

3狼狽し、心がかき乱されています。

不安に駆られ、

気分がすっかりめいっています。

ああ、私を早く元どおりにしてください。

4ああ主よ、帰って来て、私を健康にしてください。

あわれんで、お救いください。

5死んでしまっては、

友の前であなたをほめたたえることもできません。

6痛みのため、私はやせ細りました。

夜ごと涙で枕をぬらします。

7敵のために嘆き、そのために目も衰え、

かすんできました。

8不法を行う者ども、私から離れて行け。

私の泣き声は天に届き、

9訴えも聞き届けられた。

主は私の祈りにすべて答えてくださる。

10敵はみな、恥を見、

恐れにわななき、恥辱を受ける。

神は彼らに恥をかかせて

追い返します。