መዝሙር 5 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 5:1-12

መዝሙር 5

የጧት ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በዋሽንት የሚዘመር፣ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ቃሌን አድምጥ፤

መቃተቴንም ቸል አትበል።

2ንጉሤና አምላኬ ሆይ፤

ወደ አንተ እጸልያለሁና፣

ድረስልኝ ብዬ ስጮኽ ስማኝ።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ በማለዳ ድምፄን ትሰማለህ፤

በማለዳ ልመናዬን በፊትህ አቀርባለሁ፤

ፈቃድህንም በጥሞና እጠባበቃለሁ፤

4አንተ በክፋት ደስ የምትሰኝ አምላክ አይደለህም፤

ክፉም ከአንተ ጋር አያድርም።

5እብሪተኞች በፊትህ መቆም አይችሉም፤

ክፉ አድራጊዎችንም ሁሉ ጠላህ።

6ሐሰት የሚናገሩትን ታጠፋቸዋለህ፤

ደም የተጠሙትንና አታላዮችን፣

እግዚአብሔር ይጸየፋቸዋል።

7እኔ ግን በምሕረትህ ብዛት

ወደ ቤትህ እገባለሁ፤

አንተንም በመፍራት፣

ወደ ተቀደሰው መቅደስህ እሰግዳለሁ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ ከጠላቶቼ የተነሣ፣

በጽድቅህ ምራኝ፤

መንገድህንም በፊቴ አቅናልኝ።

9በንግግራቸው ውስጥ እውነት የለም፤

ልባቸው የጥፋት ጐሬ ነው፤

ጕረሯቸው የተከፈተ መቃብር ነው፤

በምላሳቸውም ይሸነግላሉ።

10አምላክ ሆይ፤ የእጃቸውን ስጣቸው!

ተንኰላቸው መውደቂያቸው ይሁን፤

ከኀጢአታቸው ብዛት የተነሣ አስወግዳቸው፣

በአንተ ላይ ዐምፀዋልና።

11አንተን መጠጊያ የሚያደርጉ ሁሉ ግን ደስ ይበላቸው፤

ዘላለም በደስታ ይዘምሩ፤

ስምህን የሚወድዱ በአንተ ደስ እንዲላቸው፣

ተከላካይ ሁንላቸው።

12እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቃንን ትባርካቸዋለህ፤

በሞገስህም እንደ ጋሻ ትከልላቸዋለህ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 5:1-12

5

1-2ああ主よ、この祈りを聞いてください。

王なる神よ、私の嘆きに耳を傾けてください。

私はあなた以外のだれにも、決して祈ったりしません。

3朝ごとに、天におられるあなたを見上げ、

御前に願い事を申し上げ、ひたすら祈ります。

4あなたは、どんな小さな悪も喜んだりなさらず、

ささいな罪でも大目に見たりはなさいません。

5ですから、おごり高ぶる罪人たちは、

あなたの鋭い視線を逃れて

罪を知られないままでいることはできません。

あなたは悪事を徹底的に憎まれるからです。

6うそはあばかれ、彼らは滅ぼされます。

主は、殺人と欺きを

どんなにお嫌いになることでしょう。

7しかしこの私は、

あわれみと愛に守られて、神殿へまいります。

心の底から恐れかしこんで神を礼拝します。

8主よ、お約束のとおり、私を導いてください。

そうでなければ、敵に踏みにじられてしまいます。

何をすればよいのか、どちらへ進むべきか、

はっきりとお教えください。

9彼らはうそばかりつき、心は悪い思いで満ちています。

彼らの誘いには罪と死の悪臭がただよいます。

彼らは甘いことばで人々を欺き、

邪悪な目的をはたそうとしています。

10ああ神よ、彼らに責任をとらせてください。

自分でしかけた罠にかからせてください。

自らの罪の重みに耐えかねて、

その下敷きになりますように。

彼らは神に背いたのですから。

11しかし、すべて神を信頼する者には、

喜びを与えてください。

神がかばってくださることを知って、

彼らがいつまでも喜びの声を上げますように。

神を愛する人たちを、幸福にひたらせてください。

12神は心から信じる者を祝福されます。

主よ、あなたは愛の盾で彼らを囲まれます。