መዝሙር 34 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 34:1-22

መዝሙር 3434 34 የዚህ መዝሙር እያንዳንዱ ጥቅስ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀመር ሲሆን፣ ጅማሬው ወይም ጅማሬውና መጨረሻው ትርጕም የሚሰጥ ግጥም ነው።

የእግዚአብሔር ፍትሕ ውዳሴ

እንደ እብድ ሆኖ አቤሜሌክ ፊት በመቅረቡ ተባርሮ በወጣ ጊዜ የዘመረው፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔርን ሁልጊዜ እባርከዋለሁ፤

ምስጋናውም ዘወትር ከአፌ አይለይም።

2ነፍሴ በእግዚአብሔር ተመካች፤

ትሑታንም ይህን ሰምተው ሐሤት ያደርጋሉ።

3ኑና ከእኔ ጋር እግዚአብሔርን አክብሩት፤

ስሙንም በአንድነት ከፍ ከፍ እናድርግ።

4እግዚአብሔርን ፈለግሁት፤ እርሱም መለሰልኝ፤

ከፍርሀቴም ሁሉ አዳነኝ።

5ወደ እርሱ የሚመለከቱ ያበራሉ፤

ፊታቸውም ከቶ አያፍርም።

6ይህ ችግረኛ ጮኸ፤ እግዚአብሔርም ሰማው፤

ከመከራውም ሁሉ አዳነው።

7እግዚአብሔርን በሚፈሩት ዙሪያ የእግዚአብሔር መልአክ ይሰፍራል፤

ያድናቸዋልም።

8እግዚአብሔር ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እዩ፤

እርሱን መጠጊያ የሚያደርግ ምንኛ ቡሩክ ነው!

9እናንተ ቅዱሳኑ፤ እግዚአብሔርን ፍሩት፤

እርሱን የሚፈሩት አንዳች አያጡምና።

10አንበሶች ሊያጡ፣ ሊራቡም ይችላሉ፤

እግዚአብሔርን የሚሹ ግን መልካም ነገር አይጐድልባቸውም።

11ልጆቼ ሆይ፣ ኑ፤ ስሙኝ፤

እግዚአብሔርን መፍራት አስተምራችኋለሁ።

12ሕይወትን የሚወድድ፣

በጎውንም ያይ ዘንድ ዕድሜን የሚመኝ ማን ነው?

13አንደበትህን ከክፉ ነገር ከልክል፤

ከንፈርህንም ከሽንገላ ጠብቅ።

14ከክፉ ሽሽ፤ መልካሙንም አድርግ፤

ሰላምን ፈልጋት፤ ተከተላትም።

15የእግዚአብሔር ዐይኖች ወደ ጻድቃን ናቸው፤

ጆሮዎቹም ለጩኸታቸው ክፍት ናቸው።

16መታሰቢያቸውን ከምድር ለማጥፋት፣

የእግዚአብሔር ፊት በክፉ አድራጊዎች ላይ ነው።

17ጻድቃን ሲጮኹ፣ እግዚአብሔር ይሰማቸዋል፤

ከመከራቸውም ሁሉ ያድናቸዋል።

18እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው፤

መንፈሳቸው የተሰበረውንም ያድናቸዋል።

19የጻድቅ መከራው ብዙ ነው፤

እግዚአብሔር ግን ከሁሉም ያድነዋል።

20ዐጥንቶቹን ሁሉ ይጠብቃል፤

ከእነርሱም አንድ አይሰበርም።

21ኀጢአተኞችን ክፋት ይገድላቸዋል፤

ጻድቃንን የሚጠሉ ይፈረድባቸዋል።

22እግዚአብሔር የባሪያዎቹን ነፍስ ይቤዣል፤

እርሱንም መጠጊያ ያደረገ አይፈረድበትም።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 34:1-22

第 34 篇

上帝的美善

大衛在亞比米勒面前裝瘋,被趕出去後,作了此詩。

1我要常常稱頌耶和華,

時刻讚美祂。

2我要誇耀祂的作為,

困苦人聽見必歡欣。

3讓我們一同頌讚祂的偉大,

尊崇祂的名!

4我向祂禱告,祂便應允我,

救我脫離一切恐懼。

5凡仰望祂的必有榮光,

不致蒙羞。

6我這可憐的人向祂呼求,

祂就垂聽,

救我脫離一切困境。

7祂的天使必四面保護敬畏祂的人,拯救他們。

8你們要親身體驗,

就知道耶和華的美善;

投靠祂的人有福了!

9耶和華的聖民啊,

你們要敬畏祂,

因為敬畏祂的人一無所缺。

10壯獅也會忍饑挨餓,

但尋求耶和華的人什麼福分都不缺。

11孩子們啊,聽我說,

我要教導你們敬畏耶和華。

12若有人熱愛生命,

渴望長壽和幸福,

13就要舌頭不出惡言,

嘴唇不說詭詐的話。

14要棄惡行善,

竭力追求和睦。

15耶和華的眼睛看顧義人,

祂的耳朵垂聽他們的呼求。

16耶和華嚴懲作惡之人,

從世上剷除他們。

17義人向耶和華呼救,祂就垂聽,

拯救他們脫離一切患難。

18祂安慰悲痛欲絕的人,

拯救心靈破碎的人。

19義人也會遭遇許多患難,

但耶和華必拯救他,

20保全他一身的骨頭,

連一根也不折斷。

21惡人必遭惡報,

與義人為敵的必被定罪。

22耶和華必救贖祂的僕人,

投靠祂的人必不被定罪。