መዝሙር 35 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

መዝሙር 35:1-28

መዝሙር 35

የተጨቈነ ሰው ጸሎት

የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ የሚታገሉኝን ታገላቸው፤

የሚዋጉኝንም ተዋጋቸው።

2ትልቁንና ትንሹን ጋሻ ያዝ፤

እኔንም ለመርዳት ተነሥ።

3በሚያሳድዱኝ ላይ፣

ጦርና ጭሬ ምዘዝ፤35፥3 ወይም …መንገድ ዝጋ

ነፍሴንም፣

“የማድንሽ እኔ ነኝ” በላት።

4ሕይወቴን የሚፈልጓት፣

ይቅለሉ፣ ይዋረዱ፤

እኔን ለማጥፋት የሚያሤሩ፣

ዐፍረው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።

5በነፋስ ፊት እንዳለ እብቅ ይሁኑ፤

የእግዚአብሔር መልአክ ያሳድዳቸው።

6መንገዳቸው ጨለማና ድጥ ይሁን፤

የእግዚአብሔር መልአክ ያባርራቸው።

7ያለ ምክንያት ወጥመዳቸውን በስውር አስቀምጠውብኛልና፤

ያለ ምክንያት ለነፍሴ ጕድጓድ ቈፍረውላታል።

8ያልታሰበ ጥፋት ይምጣባቸው፤

የሰወሩት ወጥመድ ይያዛቸው፤

ይጠፉም ዘንድ ወደ ጕድጓዱ ይውደቁ።

9ነፍሴም በእግዚአብሔር ደስ ይላታል፤

በማዳኑም ሐሤት ታደርጋለች።

10የሠራ አካላቴ እንዲህ ይልሃል፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ አንተ ማን አለ?

ድኻውን ከእርሱ ከሚበረቱ፣

ችግረኛውንና ምስኪኑን ከቀማኞች ታድናለህ።”

11ጨካኝ ምስክሮች ተነሡ፤

ስለማላውቀውም ነገር ጠየቁኝ።

12በበጎ ፈንታ ክፉ መለሱልኝ፤

ነፍሴንም ብቸኛ አደረጓት።

13እኔ ግን እነርሱ በታመሙ ጊዜ ማቅ ለበስሁ፤

ነፍሴንም በጾም አደከምኋት፤

ጸሎቴም መልስ ዐጥቶ ወደ ጕያዬ ተመለሰ።

14ለወዳጄ ወይም ለወንድሜ እንደማደርግ፣

እየተንቈራጠጥሁ አለቀስሁ፤

ለእናቴም እንደማለቅስ፣

በሐዘን ዐንገቴን ደፋሁ።

15እነርሱ ግን እኔ ስሰናከል በእልልታ ተሰበሰቡ፤

ግፈኞች በድንገት ተሰበሰቡብኝ፤

ያለ ዕረፍትም ቦጫጨቁኝ።

16እንደ ምናምንቴዎች አፌዙብኝ፤35፥16 ሰብዓ ሊቃናት እንዲሁ ሲሆን፣ በዕብራይስጥ ግን ምናምንቴ ፌዘኞች ማለት ሊሆን ይችላል።

ጥርሳቸውንም አፋጩብኝ።

17ጌታ ሆይ፤ እስከ መቼ ዝም ብለህ ታያለህ?

ነፍሴን ከክፉ ሥራቸው፣

ብርቅ ሕይወቴን ከአንበሶች ታደጋት።

18በታላቅ ጉባኤ መካከል አመሰግንሃለሁ፤

ብዙ ሕዝብ በተሰበሰበበትም አወድስሃለሁ።

19ከምድር ተነሥተው ጠላቶቼ የሆኑት፣

በላዬ ደስ አይበላቸው፤

እንዲያው የሚጠሉኝ፣

በዐይናቸው አይጣቀሱብኝ።

20የሰላም ንግግር ከአፋቸው አይወጣም፤

ዳሩ ግን በምድሪቱ በጸጥታ በሚኖሩት ላይ፣

ነገር ይሸርባሉ።

21አፋቸውን አስፍተው ከፈቱብኝ፤

“ዕሠይ! ዕሠይ! በዐይናችን አየነው” አሉ።

22እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህን አይተሃልና ዝም አትበል፤

ጌታ ሆይ፤ ከእኔ አትራቅ።

23አምላኬ፣ ጌታዬ፤ ለእኔ ለመሟገት ተነሥ!

ልትከራከርልኝም ተንቀሳቀስ።

24እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ በጽድቅህ ፍረድልኝ፤

በእኔም ላይ ደስ አይበላቸው።

25በልባቸው፣ “ዕሠይ! ያሰብነው ተሳካ!

ዋጥ አደረግነውም” አይበሉ።

26በጭንቀቴ ደስ የሚላቸው፣

ይፈሩ፤ ግራም ይጋቡ፤

በእኔ ላይ ራሳቸውን ከፍ ከፍ የሚያደርጉ፣

ዕፍረትንና ውርደትን ይከናነቡ።

27ፍትሕ ማግኘቴን የሚወድዱ፣

እልል ይበሉ፤ ሐሤትም ያድርጉ፤

ዘወትርም፣ “የባሪያው ሰላም ደስ የሚለው፣

እግዚአብሔር ከፍ ከፍ ይበል!” ይበሉ።

28አንደበቴ ጽድቅህን፣

ምስጋናህንም ቀኑን ሙሉ ይናገራል።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

詩篇 35:1-28

第 35 篇

求上帝伸冤

大衛的詩。

1耶和華啊,

求你與我的敵人為敵,

攻擊那些攻擊我的人。

2求你拿起大小盾牌來幫助我,

3舉起矛槍攻擊追趕我的人。

求你對我說:

「我是你的拯救。」

4願謀殺我的人蒙羞受辱,

謀害我的人落荒而逃!

5願耶和華的天使驅散他們,

如風吹散糠秕!

6願他們的道路漆黑泥濘,

有耶和華的天使在後追趕!

7因為他們無故設網羅,

挖陷阱要害我。

8願他們突遭禍患,

作繭自縛,自食惡果!

9我要因耶和華而歡欣,

因祂的拯救而快樂。

10我從心底發出讚歎:

耶和華啊,誰能像你?

你拯救弱者免受欺壓,

拯救窮人免遭掠奪。

11惡人誣告我,

盤問我毫無所知的事情。

12他們對我以惡報善,

令我傷心欲絕。

13他們生病時,

我披上麻衣,

謙卑地為他們禁食禱告,

但上帝沒有垂聽。

14我為他們哀傷,

視他們為朋友、弟兄;

我低頭為他們哭泣,

如同哀悼自己的母親。

15我遭遇患難時,

他們卻聚在一起幸災樂禍,

合夥誹謗我。

素不相識的人也群起攻擊我,

不住地譭謗我。

16他們肆無忌憚地嘲弄我,

咬牙切齒地憎惡我。

17耶和華啊,

你袖手旁觀要到何時?

求你救我的性命免遭殘害,

救我脫離這些獅子。

18我要在大會中稱謝你,

在眾人面前讚美你。

19求你不要讓無故攻擊我的人幸災樂禍,

不要讓無故恨我的人沾沾自喜。

20他們言語暴戾,

謀害安分守己的人。

21他們高喊:「哈哈!哈哈!

我們親眼看見了。」

22耶和華啊,這一切你都看見了,

求你不要再緘默,不要遠離我。

23我的上帝,我的主啊,

求你起來為我辯護,為我伸冤。

24我的上帝耶和華啊,

求你按你的公義宣告我無罪,

別讓他們幸災樂禍。

25別讓他們說:

「哈哈,我們如願以償了!」

別讓他們說:

「我們除掉他了!」

26願幸災樂禍的人蒙羞受辱,

自高自大的人無地自容!

27願盼望我冤屈得雪的人揚聲歡呼!

願他們常說:「耶和華當受尊崇!

祂樂意賜福給自己的僕人。」

28我要訴說你的公義,

終日讚美你。