መዝሙር 21 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 21:1-13

መዝሙር 21

ምስጋና ስለ ንጉሡ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ንጉሥ በኀይልህ ደስ ይለዋል፤

በምትሰጠውም ድል እጅግ ሐሤት ያደርጋል።

2የልቡን መሻት ሰጠኸው፤

የከንፈሮቹንም ልመና አልከለከልኸውም። ሴላ

3መልካም በረከት ይዘህ በመንገዱ ላይ ጠብቀኸው፤

የንጹሕ ወርቅ ዘውድም በራሱ ላይ ደፋህለት።

4ሕይወትን ለመነህ፤

ረዥም ዘመናትንም እስከ ዘላለም ሰጠኸው።

5በአቀዳጀኸው ድል ክብሩ ታላቅ ሆነ፤

ክብርንና ሞገስን አጐናጸፍኸው።

6ዘላለማዊ በረከትን ሰጠኸው፤

ከአንተ ዘንድ በሚገኝ ፍሥሓም ደስ አሰኘኸው፤

7ንጉሡ በእግዚአብሔር ተማምኗልና፤

ከልዑልም ጽኑ ፍቅር የተነሣ፣

ከቆመበት አይናወጥም።

8እጅህ ጠላቶችህን ሁሉ ታገኛቸዋለች፤

ቀኝ እጅህም የሚጠሉህን ፈልጋ ትይዛለች።

9በምትገለጥበት ጊዜ፣

እሳት እንደሚንቀለቀልበት ምድጃ ታደርጋቸዋለህ፤

እግዚአብሔር በመዓቱ እንዳልነበሩ ያደርጋቸዋል፤

እሳቱም ሙጥጥ አድርጋ ትበላቸዋለች።

10ዘራቸውን ከምድር፣

ዘር ማንዘራቸውንም ከሰው ልጆች መካከል ታጠፋለህ።

11ክፋት ቢያስቡብህ፣

ተንኰል ቢወጥኑብህም አይሳካላቸውም፤

12በመጡበት ትመልሳቸዋለህና፤

ቀስትህንም በፊታቸው ላይ ታነጣጥራለህ።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ በብርታትህ ከፍ ከፍ በል፤

ኀይልህን እናወድሳለን፤ እንዘምራለንም።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 21:1-13

21

1ああ主よ。

王はどんなにあなたの御力を喜ぶことでしょう。

救われたことを、どれほど喜ぶことでしょう。

2主が願いをかなえ、

望むものをことごとくお与えになったからです。

3主は、名誉と繁栄が保証された王座に彼を迎え、

純金の王冠をかぶせてくださいました。

4満ち足りた長寿を求める王の願いを

聞き届けられました。

彼のいのちは永遠に限りなく続くのです。

5主は彼に名誉と名声を与え、

威光と尊厳とをまとわせました。

6また、永遠の幸福を授け、

主の前に立つことの喜びが、

いつまでも薄れないようにしてくださいました。

7王は主により頼んでいるので、

つまずいたり倒れたりすることは絶対にありません。

あらゆる神々にまさる神の変わらない愛に、

頼りきっているからです。

8ああ主よ。あなたの手は敵を見つけ出します。

主を憎む者を一人残らず探し出します。

9-10主が姿を現されると、御前から出る激しい火が、

彼らをたちどころに滅ぼします。

その子らも共に倒されます。

11彼らは、主であるあなたに陰謀を企んだからです。

しかし、そんな計画が成功するはずはありません。

12彼らは、主の矢にねらわれているのを知り、

あわてて向きを変え、一目散に逃げるでしょう。

13ああ主よ、この賛美をお受けください。

御力を賛美しているのですから。

私たちは主の力強いみわざをたたえて、

賛美の歌を歌いましょう。