መዝሙር 20 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 20:1-9

መዝሙር 20

ጸሎት ለንጉሡ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር በጭንቅ ቀን ይስማህ፤

የያዕቆብም አምላክ ስም ይጠብቅህ።

2ከመቅደሱ ረድኤት ይላክልህ፤

ከጽዮንም ደግፎ ይያዝህ።

3ቍርባንህን ሁሉ ያስብልህ፤

የሚቃጠል መሥዋዕትህን ይቀበልልህ። ሴላ

4የልብህን መሻት ይስጥህ፤

ዕቅድህን ሁሉ ያከናውንልህ።

5በአንተ ድል ደስ ይበለን፤

በአምላካችን ስም አርማችንን ከፍ እናደርጋለን፤

እግዚአብሔር የለመንኸውን ሁሉ ይፈጽምልህ።

6እግዚአብሔር፣ የቀባውን እንደሚያድን

አሁን ዐወቅሁ፤

የማዳን ኀይል ባለው ቀኝ እጁ፣

ከተቀደሰው ሰማይ ይመልስለታል።

7እነዚህ በሰረገላ፣ እነዚያ በፈረስ ይመካሉ፤

እኛ ግን ትምክሕታችን የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም ነው።

8እነርሱ ተሰነካክለው ወደቁ፤

እኛ ግን ተነሣን፤ ጸንተንም ቆምን።

9እግዚአብሔር ሆይ፤ ንጉሥን አድን፤

እኛም በጠራንህ ቀን ስማን።20፥9 ወይም አድን! ንጉሥ ሆይ፤ ስማን

Japanese Contemporary Bible

詩篇 20:1-9

20

1苦難の日に、主があなたとともにおられますように。

ヤコブの神が、いっさいの危険から

守ってくださいますように。

2主がシオンの聖所から、

助けの手を伸べてくださいますように。

3あなたのささげ物、焼き尽くすいけにえを、

喜んで心に留めてくださいますように。

4あなたの願いをかなえ、

計画をことごとく実現させてくださいますように。

5あなたの勝利の知らせが伝わると、

喜びの声がわき上がり、

神があなたのためになさったすべてを記念して、

神をたたえる旗が高く掲げられますように。

あなたの祈りが、すべて答えられますように。

6主が王をお救いになることを、今こそ知りました。

主は高い天から答えて、

大勝利をもたらしてくださいます。

7国々は軍隊や武器を誇りますが、

私たちは私たちの神、主を誇ります。

8国々はやがて衰え、滅びます。

しかし、私たちは立ち上がり、

大地に根を下ろして、しっかりと立ち続けます。

9ああ主よ、王に勝利をお与えください。

どうか、この祈りをお聞きください。