መዝሙር 19 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 19:1-14

መዝሙር 19

እግዚአብሔር የጽድቅ ፀሓይ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፤

የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያውጃሉ።

2ቀን ለሌላው ቀን ይናገራል፤

ሌሊትም ለሌሊት ዕውቀትን ይገልጣል፤

3ንግግር የለም፤ ቃል የለም፤

ድምፃቸው በጆሮ የሚሰማ አይደለም።19፥3 ወይም የሚናገሩት የላቸውም፤ ቃላት የለም፤ ከእርሱ ምንም ድምፅ አይሰማም

4ያም ሆኖ ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ፣

ቃላቸውም19፥4 ሰብዓ ሊቃናት የሩምና ሱርስት እንዲሁ ሲሆኑ፣ ዕብራይስጡ ግን ድንበራቸው ይላል። እስከ ዓለም ዳርቻ ይወጣል።

እርሱ በሰማያት ለፀሓይ ድንኳን ተክሏል፤

5ፀሓይም ከእልፍኙ እንደሚወጣ ሙሽራ ይወጣል፤

ወደ ግቡም እንደሚሮጥ ብርቱ ሰው ደስ ይለዋል።

6መውጫው ከሰማያት ዳርቻ ነው፤

ዑደቱም እስከ ሌላኛው ዳርቻ ነው፤

ከትኵሳቱም የሚሰወር የለም።

7የእግዚአብሔር ሕግ ፍጹም ነው፤

ነፍስንም መልሶ ያለመልማል፤

የእግዚአብሔር ሥርዐት የታመነ ነው፤

አላዋቂውን ጥበበኛ ያደርጋል።

8የእግዚአብሔር ሕግጋት ትክክል ናቸው፤

ልብን ደስ ያሰኛሉ።

የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው፤

ዐይንን ያበራል።

9እግዚአብሔርን መፍራት ንጹሕ ነው፤

ለዘላለም ጸንቶ ይኖራል።

የእግዚአብሔር ፍርድ የታመነ፣

ሁለንተናውም ጻድቅ ነው፤

10ከወርቅ ይልቅ የከበረ፣

እጅግ ከጠራ ወርቅም የተሻለ ነው፤

ከማር ይልቅ ይጣፍጣል፤

ከማር ወለላም ይበልጥ ይጥማል።

11ደግሞም አገልጋይህ በእርሱ ጥንቃቄ ያደርጋል፤

እርሱንም መጠበቅ ወሮታ አለው።

12ስሕተቱን ማን ሊያስተውል ይችላል?

ከተሰወረ በደል አንጻኝ።

13ባሪያህን ከድፍረት ኀጢአት ጠብቅ፤

እንዳይሠለጥንብኝም ርዳኝ፤

ያን ጊዜ ያለ እንከን እሆናለሁ፤

ከታላቅ በደልም እነጻለሁ።

14መጠጊያዬና አዳኜ እግዚአብሔር ሆይ፤

የአፌ ቃልና የልቤ ሐሳብ፣

በፊትህ ያማረ ይሁን።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 19:1-14

19

1天は、神の栄光を物語る、神の手による傑作です。

2天は、昼となく夜となく、神について語り続けます。

3-4大空は、音もことばもなく静まり返っているのに、

大空が語っていることは全世界に知られます。

太陽は天の神の定めた場所に住んでいます。

5太陽はその場所から出て、

結婚式の花婿のように晴れ晴れと、

また、競技を前にした選手のように、

意気揚々と大空を闊歩します。

6天の端から端まで行き巡り、

その熱を免れるものは何一つありません。

7-8主のおきては完全で、私たちを守り、

賢くし、喜びと光を与えます。

9主のおきては純粋で正しく、変わることがありません。

10また、金よりも慕わしく、

みつばちの巣からしたたるみつよりも甘いのです。

11主のおきては、危険に近づかないように警告し、

従う者には祝福を約束します。

12しかし人は、心にひそむ罪を

どうして知ることができましょう。

どうか、隠れた罪からきよめてください。

13故意に悪に走ることからも引き止め、守ってください。

そうすれば、私は過ちを犯さず、

大きな罪からも逃れることができます。

14私の口のことばと、秘めた思いが、

神に喜ばれますように。

ああ、私の岩、私の救い主、主よ。