መዝሙር 148 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 148:1-14

መዝሙር 148

ፍጥረተ ዓለም ሁሉ ያመስግን

1ሃሌ ሉያ።148፥1 አንዳንዶች ከ14 ጭምር እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

እግዚአብሔርን ከሰማያት አመስግኑት፤

በላይ በአርያም አመስግኑት።

2መላእክቱ ሁሉ አመስግኑት፤

ሰራዊቱ ሁሉ አመስግኑት፤

3ፀሓይና ጨረቃ አመስግኑት፤

የምታበሩ ከዋክብት ሁሉ አመስግኑት።

4ሰማየ ሰማያት አመስግኑት፤

ከሰማያትም በላይ ያላችሁ ውሆች አወድሱት።

5እርሱ ስላዘዘ ተፈጥረዋልና፣

የእግዚአብሔርን ስም ያመስግኑት።

6ከዘላለም እስከ ዘላለም አጸናቸው፤

የማይሻርም ሕግ ደነገገላቸው።

7የባሕር ውስጥ ግዙፍ ፍጥረትና ጥልቅ ውሆች ሁሉ፣

እግዚአብሔርን ከምድር አመስግኑት።

8እሳትና በረዶ፣ ዐመዳይና ጭጋግ፣

ትእዛዙንም የሚፈጽም ዐውሎ ነፋስ፣

9ተራሮችና ኰረብቶች ሁሉ፣

የፍሬ ዛፎችና ዝግቦች ሁሉ፣

10የዱር አራዊትና የቤት እንስሳት ሁሉ፣

በምድር የሚሳቡ ፍጥረታትና የሚበርሩ ወፎችም፣

11የምድር ነገሥታትና ሕዝቦች ሁሉ፣

መሳፍንትና የምድር ገዦች ሁሉ፣

12ወጣት ወንዶችና ደናግል፣

አረጋውያንና ልጆች ያመስግኑት።

13ስሙ ብቻውን ከፍ ያለ ነውና፣

ክብሩም ከምድርና ከሰማይ በላይ ነውና፣

እነዚህ ሁሉ የእግዚአብሔርን ስም ያመስግኑ።

14እርሱ ለሕዝቡ ቀንድን148፥14 ቀንድ የጥንካሬ ትእምርት ሲሆን፣ ንጉሥን ያመለክታል። አስነሥቷል፤

ለቅዱሳኑ ሁሉ ምስጋና፣

እጅግ ቅርቡ ለሆነው ሕዝቡ፣ ለእስራኤል ልጆች።

ሃሌ ሉያ።

Ketab El Hayat

مزمور 148:1-14

الْمَزْمُورُ الْمِئَةُ وَالثَّامِنُ وَالأَرْبَعُونَ

1هَلِّلُويَا! سَبِّحُوا الرَّبَّ مِنَ السَّمَاوَاتِ. سَبِّحُوهُ فِي الأَعَالِي. 2سَبِّحُوهُ يَا جَمِيعَ مَلائِكَتِهِ. سَبِّحُوهُ يَا جَمِيعَ أَجْنَادِهِ. 3سَبِّحِيهِ يَا شَمْسُ وَيَا قَمَرُ. سَبِّحِيهِ يَا جَمِيعَ الكَوَاكِبِ المُشْرِقَةِ. 4سَبِّحِيهِ يَا سَمَاءَ السَّمَاوَاتِ، وَيَا أَيَّتُهَا السُّحُبُ الَّتِي فَوْقَ الجَلَدِ. 5لِتُسَبِّحْ هَذِهِ اسْمَ الرَّبِّ، لأَنَّهَا بِأَمْرِهِ خُلِقَتْ، 6وَثَبَّتَهَا إِلَى الدَّهْرِ وَالأَبَدِ، وَاضِعاً لَهَا حَدّاً لَا تَتَجَاوَزُهُ.

7سَبِّحِي الرَّبَّ مِنْ عَلَى الأَرْضِ يَا وُحُوشَ الْبَحْرِ وَيَا كُلَّ اللُّجَجِ. 8أَيَّتُهَا النَّارُ وَالْبَرَدُ، وَالثَّلْجُ والضَّبَابُ، الرِّيحُ الْعَاصِفَةُ الْمُنَفِّذَةُ لأَمْرِهِ، 9الْجِبَالُ وَالتِّلالُ جَمِيعاً، الأَشْجَارُ الْمُثْمِرَةُ وَالأَرْزُ كُلُّهُ، 10الْحَيْوَانَاتُ الْبَرِّيَّةُ وَالْمَوَاشِي كُلُّهَا، الزَّوَاحِفُ وَالطُّيُورُ. 11مُلُوكُ الأَرْضِ وَجَمِيعُ الشُّعُوبِ وَحُكَّامُ الأَرْضِ وَجَمِيعُ الرُّؤَسَاءِ، 12الْفِتْيَانُ وَالْفَتَيَاتُ وَالشُّيُوخُ وَالشُّبَّانُ، 13لِيُسَبِّحُوا اسْمَ الرَّبِّ، لأَنَّهُ وَحْدَهُ مُتَعَالٍ. مَجْدُهُ فَوْقَ الأَرْضِ وَالسَّمَاوَاتِ. 14يَرْفَعُ رَأْسَ شَعْبِهِ إِكْرَاماً لِكُلِّ أَتْقِيَائِهِ، لِبَنِي إِسْرَائِيلَ الشَّعْبِ الْمُقَرَّبِ إِلَيْهِ. هَلِّلُويَا.