መዝሙር 147 – NASV & NAV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 147:1-20

መዝሙር 147

መዝሙር ለሁሉን ቻይ አምላክ

1ሃሌ ሉያ።147፥1 አንዳንዶች ከ20 ጭምር እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

አምላካችንን በመዝሙር ማወደስ እንዴት መልካም ነው!

እርሱን ማመስገን ደስ ያሰኛል፤ ይህ ተገቢም ነው።

2እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን መልሶ ይሠራታል፤

ከእስራኤል የተበተኑትን ይሰበስባል።

3ልባቸው የተሰበረውን ይፈውሳል፤

ቍስላቸውንም ይጠግናል።

4የከዋክብትን ብዛት ያውቃል፤

እያንዳንዱንም በስሙ ይጠራዋል።

5ጌታችን ታላቅ ነው፤ እጅግ ኀያልም ነው፤

ለጥበቡም ወሰን የለውም።

6እግዚአብሔር ትሑታንን ከፍ ያደርጋል፤

ክፉዎችን ግን ወደ ምድር ይጥላል።

7ለእግዚአብሔር በምስጋና ዘምሩ፤

ለአምላካችንም በመሰንቆ ምስጋና አቅርቡ።

8ሰማይን በደመናት የሚሸፍን እርሱ ነው፤

ለምድርም ዝናብን ይሰጣል፤

በተራሮችም ላይ ሣር ያበቅላል።

9ለእንስሳት ምግባቸውን፣

የቍራ ጫጩቶችም ሲንጫጩ የሚበሉትን ይሰጣቸዋል።

10እርሱ በፈረስ ኀይል አይደሰትም፤

በሯጭም ብርታት ላይ ደስታውን አያደርግም።

11ነገር ግን እግዚአብሔር በሚፈሩት፣

በምሕረቱ በሚታመኑትም ይደሰታል።

12ኢየሩሳሌም ሆይ፤ እግዚአብሔርን አመስግኚ፤

ጽዮን ሆይ፤ አምላክሽን አወድሺ፤

13እርሱ የደጆችሽን መወርወሪያ አጽንቷልና፤

ልጆችሽንም በውስጥሽ ባርኳል።

14በድንበርሽ ውስጥ ሰላም ያሰፍናል፤

ማለፊያ ስንዴም ያጠግብሻል።

15ትእዛዙን ወደ ምድር ይልካል፤

ቃሉም እጅግ በፍጥነት ይሮጣል።

16ዐመዳዩን እንደ በርኖስ ይዘረጋል፤

ውርጩን እንደ ዐመድ ይነሰንሳል።

17የበረዶውን ድንጋይ ቍልቍል ይወረውረዋል፤

በውሽንፍሩስ ቅዝቃዜ ፊት ማን ሊቆም ይችላል?

18ቃሉን ልኮ ያቀልጣቸዋል፤ ነፋሱን ያነፍሳል፤ ውሆችንም ያፈስሳል።

19ቃሉን ለያዕቆብ፣

ሥርዐቱንና ፍርዱን ለእስራኤል ይገልጣል።

20ይህን ለማንኛውም ሌላ ሕዝብ አላደረገም፤

እነርሱም ፍርዱን አላወቁም።

ሃሌ ሉያ።

Ketab El Hayat

مزمور 147:1-20

الْمَزْمُورُ الْمِئَةُ وَالسَّابِعُ وَالأَرْبَعُونَ

1سَبِّحُوا الرَّبَّ، فَإِنَّ التَّرَنُّمَ لإِلَهِنَا طَيِّبٌ، وَتَسْبِيحُهُ مُلِذٌّ وَلائِقٌ. 2يَبْنِي الرَّبُّ أُورُشَلِيمَ، وَيَجْمَعُ شَمْلَ الْمَنْفِيِّينَ مِنْ إِسْرَائِيلَ. 3إِنَّهُ يَشْفِي مُنْكَسِرِي الْقَلْبِ وَيُضَمِّدُ جِرَاحَهُمْ. 4يُحْصِي عَدَدَ الْكَوَاكِبِ وَيَدْعُوهَا جَمِيعَهَا بِأَسْمَائِهَا. 5عَظِيمٌ هُوَ سَيِّدُنَا، وَفَائِقَةٌ هِيَ قُوَّتُهُ، وَلَا حَدَّ لِحِكْمَتِهِ. 6يَرْفَعُ الرَّبُّ الْوُدَعَاءَ، وَيَطْرَحُ الأَشْرَارَ إِلَى الأَرْضِ.

7رُدُّوا عَلَى الرَّبِّ بِحَمْدٍ، رَنِّمُوا لإِلَهِنَا عَلَى الْعُودِ. 8فَهُوَ يَكْسُو السَّمَاوَاتِ سَحَاباً وَيُمْطِرُ عَلَى الأَرْضِ، وَيُنْبِتُ الْعُشْبَ عَلَى الْجِبَالِ. 9يَهَبُ الطَّعَامَ لِلْبَهَائِمِ، وَلِفِرَاخِ الْغِرْبَانِ النَّاعِقَةِ. 10لَا تَسْتَهْوِيهِ قُوَّةُ الْخَيْلِ، وَلَا تَسُرُّهُ سَاقَا الْعَدَّاءِ. 11إِنَّمَا يَرْضَى الرَّبُّ بِخَائِفِيهِ، الرَّاجِينَ رَحْمَتَهُ.

12مَجِّدِي الرَّبَّ يَا أُورُشَلِيمُ، وَسَبِّحِي إِلَهَكِ يَا صِهْيَوْنُ. 13فَإِنَّهُ ثَبَّتَ عَوَارِضَ أَبْوَابِكِ (فِي وَجْهِ الأَعْدَاءِ)، وَبَارَكَ بَنِيكِ فِي دَاخِلِكِ. 14هُوَ الَّذِي يَجْعَلُ حُدُودَكِ آمِنَةً، وَمِنْ أَفْضَلِ الْحِنْطَةِ يُشْبِعُكِ خُبْزاً. 15يُصْدِرُ أَمْرَهُ إِلَى الأَرْضِ فَتُنَفِّذُهُ بِسُرْعَةٍ فَائِقَةٍ. 16يَنْثُرُ الثَّلْجَ كَالصُّوفِ، وَيُذَرِّي الْجَلِيدَ كَالرَّمَادِ. 17يُلْقِي بَرَدَهُ كَفُتَاتِ الْخُبْزِ. مَنْ يَصْمُدُ فِي وَجْهِ صَقِيعِهِ؟ 18ثُمَّ يُصْدِرُ أَمْرَهُ فَيُذِيبُهَا. يُرْسِلُ رِيحَهُ فَتَسِيلُ الْمِيَاهُ. 19يُعْلِنُ لِيَعْقُوبَ كَلِمَتَهُ وَلإِسْرَائِيلَ فَرَائِضَهُ وَأَحْكَامَهُ. 20لَمْ يُعَامِلْ أُمَّةً أُخْرَى هَكَذَا، وَلَمْ يُعَرِّفْهَا أَحْكَامَهُ هَلِّلُويَا.