መዝሙር 144 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 144:1-15

መዝሙር 144

የጦርነት መዝሙር

የዳዊት መዝሙር።

1እጆቼን ለጦርነት፣ ጣቶቼን ለውጊያ የሚያሠለጥን፣

እግዚአብሔር ዐለቴ ይባረክ።

2እርሱ አፍቃሪ አምላኬና ጽኑ ዐምባዬ ነው፤

ምሽጌና ታዳጊዬ፣

የምከለልበትም ጋሻዬ ነው፤

ሕዝቤን የሚያስገዛልኝም144፥2 አንዳንዶች ሕዝቦችን የሚያሰገዛልኝ ይላሉ። እርሱ ነው።

3እግዚአብሔር ሆይ፤ ይህን ያህል በልብህ ስፍራ ትሰጠው ዘንድ ሰው ምንድን ነው?

ታስበውስ ዘንድ የሰው ልጅ እስከዚህ ምንድን ነው?

4ሰው እንደ እስትንፋስ ነው፤

ዘመኑም ፈጥኖ እንደሚያልፍ ጥላ ነው።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ሰማያትህን ሰንጥቀህ ውረድ፤

ይጤሱም ዘንድ ተራሮችን ዳስስ።

6የመብረቅ ብልጭታ ልከህ በትናቸው፤

ፍላጻህን ሰድደህ ግራ አጋባቸው።

7እጅህን ከላይ ዘርጋ፤

ከኀይለኛ ውሃ፣

ከባዕዳንም እጅ

ታደገኝ፤ አድነኝም።

8አንደበታቸው ሐሰትን ይናገራል፤

ቀኝ እጃቸውም የቅጥፈት ቀኝ እጅ ናት።

9አምላክ ሆይ፤ አዲስ ቅኔ እቀኝልሃለሁ፤

ዐሥር አውታር ባለው በገና እዘምርልሃለሁ።

10ነገሥታትን ድል የሚያጐናጽፍ፣

ባሪያውን ዳዊትን ከሚጐዳ ሰይፍ የሚያድነው እርሱ ነው።

11አንደበታቸው ሐሰትን ከሚናገር፣

ቀኝ እጃቸው የቅጥፈት ቀኝ እጅ ከሆነችው፣

ከባዕዳን እጅ

ታደገኝ፤ አድነኝም።

12ወንዶች ልጆቻችን በወጣትነታቸው፣

የተሟላ ዕድገት እንዳገኘ ተክል፣

ሴቶች ልጆቻችንም ቤተ መንግሥት ለማስጌጥ

እንደ ተቀረጹ የማእዘን ዐምዶች ይሁኑ።

13ጐተራዎቻችን በተለያየ የእህል ዐይነት፣

የተሞሉ ይሁኑ፤

በጎቻችን እስከ ሺሕ ይውለዱ፤

በመስኮቻችንም እስከ ዐሥር ሺሕ ይባዙ።

14ከብቶቻችን ይክበዱ፤144፥14 ወይም መሪዎቻችን ይጠነክራሉ

አይጨንግፉ፤ አይጥፉም።

እኛም በምርኮ አንወሰድ፤

በአደባባዮቻችንም ዋይታ አይሰማ።

15ይህ ባርኮት ገንዘቡ የሆነ ሕዝብ ምስጉን ነው፤

እግዚአብሔር አምላኩ የሆነ ሕዝብ ምስጉን ነው።

King James Version

Psalms 144:1-15

A Psalm of David.

1Blessed be the LORD my strength, which teacheth my hands to war, and my fingers to fight:144.1 strength: Heb. rock144.1 to war…: Heb. to the war, etc

2My goodness, and my fortress; my high tower, and my deliverer; my shield, and he in whom I trust; who subdueth my people under me.144.2 My goodness: or, My mercy

3LORD, what is man, that thou takest knowledge of him! or the son of man, that thou makest account of him!

4Man is like to vanity: his days are as a shadow that passeth away.

5Bow thy heavens, O LORD, and come down: touch the mountains, and they shall smoke.

6Cast forth lightning, and scatter them: shoot out thine arrows, and destroy them.

7Send thine hand from above; rid me, and deliver me out of great waters, from the hand of strange children;144.7 hand from: Heb. hands from

8Whose mouth speaketh vanity, and their right hand is a right hand of falsehood.

9I will sing a new song unto thee, O God: upon a psaltery and an instrument of ten strings will I sing praises unto thee.

10It is he that giveth salvation unto kings: who delivereth David his servant from the hurtful sword.144.10 salvation: or, victory

11Rid me, and deliver me from the hand of strange children, whose mouth speaketh vanity, and their right hand is a right hand of falsehood:

12That our sons may be as plants grown up in their youth; that our daughters may be as corner stones, polished after the similitude of a palace:144.12 polished: Heb. cut

13That our garners may be full, affording all manner of store: that our sheep may bring forth thousands and ten thousands in our streets:144.13 all…: Heb. from kind to kind

14That our oxen may be strong to labour; that there be no breaking in, nor going out; that there be no complaining in our streets.144.14 strong…: Heb. able to bear burdens, or, loaden with flesh

15Happy is that people, that is in such a case: yea, happy is that people, whose God is the LORD.