መዝሙር 145 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 145:1-21

መዝሙር 145145 ይህ መዝሙር ተከታታይ በሆኑ የዕብራይስጥ ፊደላት የሚጀምር ሲሆን፣ (ከ13 ጭምር) መነሻዎቹ ወይም መነሻዎቹና መድረሻዎቹ ሆህያት ቍልቍል ሲነበቡ ትርጕም ያላቸውን ቃላት የሚፈጥሩ ናቸው።

ምስጋና ለንጉሡ ለእግዚአብሔር

የዳዊት የምስጋና መዝሙር።

1አምላኬና ንጉሤ ሆይ፤ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ፤

ስምህን ከዘላለም እስከ ዘላለም እባርካለሁ።

2በየቀኑ እባርክሃለሁ፤

ስምህንም ከዘላለም እስከ ዘላለም አመሰግናለሁ።

3እግዚአብሔር ታላቅ ነው፤ እጅግ ሊመሰገንም ይገባዋል፤

ታላቅነቱም አይመረመርም።

4ሥራህን አንዱ ትውልድ ለሌላው ትውልድ ያስተጋባል፤

ብርቱ ሥራህን ያውጃል።

5ስለ ግርማህ ውበትና ክብር ይናገራሉ፤

ስለ ድንቅ ሥራህም145፥5 የሙት ባሕር ጥቅልሎች እና ሱርስት (የሰብዓ ሊቃናትን ትርጕም ይመ) ስለ ግርማህ ታላቅነትና ክብር፣ ዕፁብ ድንቅ ሥራህን አሰላስላለሁ ይላሉ። ያወራሉ።

6ስለ ድንቅ ሥራህ ብርታት ይነጋገራሉ፤

እኔም ስለ ታላቅነትህ ዐውጃለሁ።

7የበጎነትህን ብዛት በደስታ ያወሳሉ፤

ስለ ጽድቅህም በእልልታ ይዘምራሉ።

8እግዚአብሔር ቸር ነው፤ ርኅሩኅም ነው፤

ለቍጣ የዘገየ፣ ምሕረቱ የበዛ።

9እግዚአብሔር ለሁሉ ቸር ነው፤

ምሕረቱም በፍጥረቱ ሁሉ ላይ ነው።

10እግዚአብሔር ሆይ፤ ፍጥረትህ ሁሉ ያመሰግንሃል፤

ቅዱሳንህም ይባርኩሃል።

11ስለ መንግሥትህ ክብር ይናገራሉ፤

ስለ ኀይልህም ይነጋገራሉ፤

12በዚህም ብርቱ ሥራህን፣

የመንግሥትህንም ግርማ ክብር ያስታውቃሉ።

13መንግሥትህ የዘላለም መንግሥት ናት፤

ግዛትህም ለትውልድ ሁሉ ጸንቶ ይኖራል።

እግዚአብሔር ቃሉን ሁሉ ይጠብቃል፤

በሥራውም145፥13 አንድ የማስሬቲክ ቅጅ፣ የሙት ባሕር ጥቅልሎች እና ሱርስት (የሰብዓ ሊቃናትን ትርጕም ይመ) እንዲሁም አብዛኛው የማስሬቲክ ቅጆች የ13 ሁለት ስንኞች የሏቸውም። ሁሉ ቸር ነው።

14እግዚአብሔር የሚንገዳገዱትን ሁሉ ይደግፋል፤

የወደቁትንም ሁሉ ያነሣል።

15የሁሉ ዐይን አንተን በተስፋ ይጠብቃል፤

አንተም ምግባቸውን በወቅቱ ትሰጣቸዋለህ።

16አንተ እጅህን ትዘረጋለህ፤

የሕያዋን ፍጥረታትንም ሁሉ ፍላጎት ታረካለህ።

17እግዚአብሔር በመንገዱ ሁሉ ጻድቅ፣

በሥራውም ሁሉ ቸር ነው።

18እግዚአብሔር ለሚጠሩት ሁሉ፣

በእውነት ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው።

19ለሚፈሩት ፍላጎታቸውን ይፈጽማል፤

ጩኸታቸውን ይሰማል፤ ያድናቸዋልም።

20እግዚአብሔር የሚወድዱትን ሁሉ ይጠብቃል፤

ክፉዎችን ሁሉ ግን ያጠፋል።

21አፌ የእግዚአብሔርን ምስጋና ይናገራል፤

ፍጡር ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም፣ ቅዱስ ስሙን ይባርክ።

King James Version

Psalms 145:1-21

David’s Psalm of praise.

1I will extol thee, my God, O king; and I will bless thy name for ever and ever.

2Every day will I bless thee; and I will praise thy name for ever and ever.

3Great is the LORD, and greatly to be praised; and his greatness is unsearchable.145.3 and his…: Heb. and of his greatness there is no search

4One generation shall praise thy works to another, and shall declare thy mighty acts.

5I will speak of the glorious honour of thy majesty, and of thy wondrous works.145.5 works: Heb. things, or, words

6And men shall speak of the might of thy terrible acts: and I will declare thy greatness.145.6 declare: Heb. declare it

7They shall abundantly utter the memory of thy great goodness, and shall sing of thy righteousness.

8The LORD is gracious, and full of compassion; slow to anger, and of great mercy.145.8 of great…: Heb. great in mercy

9The LORD is good to all: and his tender mercies are over all his works.

10All thy works shall praise thee, O LORD; and thy saints shall bless thee.

11They shall speak of the glory of thy kingdom, and talk of thy power;

12To make known to the sons of men his mighty acts, and the glorious majesty of his kingdom.

13Thy kingdom is an everlasting kingdom, and thy dominion endureth throughout all generations.145.13 an…: Heb. a kingdom of all ages

14The LORD upholdeth all that fall, and raiseth up all those that be bowed down.

15The eyes of all wait upon thee; and thou givest them their meat in due season.145.15 wait…: or, look unto

16Thou openest thine hand, and satisfiest the desire of every living thing.

17The LORD is righteous in all his ways, and holy in all his works.145.17 holy: or, merciful, or, bountiful

18The LORD is nigh unto all them that call upon him, to all that call upon him in truth.

19He will fulfil the desire of them that fear him: he also will hear their cry, and will save them.

20The LORD preserveth all them that love him: but all the wicked will he destroy.

21My mouth shall speak the praise of the LORD: and let all flesh bless his holy name for ever and ever.