መዝሙር 142 – NASV & HTB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 142:1-7

መዝሙር 142

የሚታደን ሰው ጸሎት

ዋሻ ውስጥ በነበረ ጊዜ፤ የዳዊት ትምህርት፤142 ርእሱ ላይ ሥነ ጽሑፋዊ ወይም የዜማ ቃል ሊሆን ይችላል። ጸሎት።

1ድምፄን ከፍ አድርጌ ወደ እግዚአብሔር እጮኻለሁ፤

ድምፄን ከፍ አድርጌ ወደ እግዚአብሔር ልመና አቀርባለሁ።

2ብሶቴን በፊቱ አፈስሳለሁ፤

ችግሬንም በፊቱ እናገራለሁ።

3መንፈሴ በውስጤ ሲዝል፣

መንገዴን የምታውቅ አንተ ነህ፤

በመተላለፊያ መንገዴ ላይ፣

ወጥመድ በስውር ዘርግተውብኛል።

4ወደ ቀኜ ተመልከት፤ እይም፤

ስለ እኔ የሚገድደው የለም፤

ማምለጫም የለኝም፤

ስለ ነፍሴም ደንታ ያለው የለም።

5እግዚአብሔር ሆይ፤ ወደ አንተ እጮኻለሁ፤

ደግሞም፣ “አንተ መጠጊያዬ ነህ፤

በሕያዋንም ምድር ዕድል ፈንታዬ ነህ” እላለሁ።

6እጅግ ተስፋ ቈርጫለሁና፣

ጩኸቴን ስማ፤

ከዐቅም በላይ ሆነውብኛልና፣

ከሚያሳድዱኝ አድነኝ።

7ስምህን አመሰግን ዘንድ፣ ነፍሴን ከወህኒ አውጣት፤

ከምታደርግልኝም በጎ ነገር የተነሣ፣

ጻድቃን በዙሪያዬ ይሰበሰባሉ።

Het Boek

Psalmen 142:1-8

1Een leerzaam gedicht van David. Hij schreef dit gebed toen hij zich in de grot verborg.

2Hardop roep ik naar de Here

en ik smeek Hem naar mij te luisteren.

3Ik stort mijn hele hart voor Hem uit,

al mijn ellende vertel ik Hem.

4Als alles mij te veel wordt,

weet U hoe ik verder moet.

Men zet vallen voor mij op het pad dat ik moet gaan.

5Ik kijk naar rechts en zie uit naar hulp,

maar geen mens kijkt naar mij om.

Ik heb geen plek om te schuilen

en niemand vraagt hoe het met mij gaat.

6Here, ik roep naar U:

‘U bent de beste plaats om te schuilen.

U houdt mij in leven.

7Luister naar mijn smeekgebed,

ik ben zo verzwakt.

Bevrijd mij van de vijanden

die mij achtervolgen,

zij zijn veel sterker dan ik.

8Leid mij uit deze diepe ellende,

dan zal ik uw naam prijzen.

Als U mij redt,

zullen oprechte mensen om mij heen komen staan.’