መዝሙር 139 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 139:1-24

መዝሙር 139

ሁሉን ዐዋቂ አምላክ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ መረመርኸኝ፤

ደግሞም ዐወቅኸኝ።

2አንተ መቀመጤንና መነሣቴን ታውቃለህ፤

የልቤንም ሐሳብ ገና ከሩቁ ታስተውላለህ።

3መሄድ መተኛቴን አጥርተህ ታውቃለህ፤

መንገዶቼንም ሁሉ ተረድተሃቸዋል።

4እግዚአብሔር ሆይ፤ ገና ቃል ከአንደበቴ ሳይወጣ፣

እነሆ፤ አንተ ሁሉንም ታውቃለህ።

5አንተ ከኋላም ከፊትም ዙሪያዬን ከለልኸኝ፤

እጅህንም በላዬ አደረግህ።

6እንዲህ ያለው ዕውቀት ለእኔ ድንቅ ነው፤

ልደርስበትም የማልችል ከፍ ያለ ነው።

7ከመንፈስህ ወዴት እሄዳለሁ?

ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ?

8ወደ ሰማይ ብወጣ፣ አንተ በዚያ አለህ፤

መኝታዬንም በሲኦል139፥8 አንዳንድ ትርጕሞች በጥልቁ ውስጥ ይላሉ። ባደርግ በዚያ ትገኛለህ።

9በንጋት ክንፍ ተነሥቼ ብበርር፣

እስከ ባሕሩ ዳርቻ መጨረሻ ብሄድ፣

10በዚያም ቢሆን እጅህ ትመራኛለች፤

ቀኝ እጅህም አጥብቃ ትይዘኛለች።

11እኔም፣ “ጨለማው በርግጥ ይሰውረኛል፤

በዙሪያዬ ያለውም ብርሃን ሌሊት ይሆናል” ብል፣

12ጨለማ የአንተን ዐይን አይዝም፤

ሌሊቱም እንደ ቀን ያበራል፤

ጨለማም ብርሃንም ለአንተ አንድ ናቸውና።

13አንተ ውስጣዊ ሰውነቴን ፈጥረሃልና፤

በእናቴም ማሕፀን ውስጥ አበጃጅተህ ሠራኸኝ።

14ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ፤

ሥራህ ድንቅ ነው፤

ነፍሴም ይህን በውል ተረድታለች።

15እኔ በስውር በተሠራሁ ጊዜ፣

ዐጥንቶቼ ከአንተ አልተደበቁም፤

በምድር ጥልቀት ውስጥ በጥበብ በተሠራሁ ጊዜ፣

16ዐይኖችህ ገና ያልተበጀውን አካሌን አዩ፤

ለእኔ የተወሰኑልኝም ዘመናት፣

ገና አንዳቸው ወደ መኖር ሳይመጡ፣

በመጽሐፍ ተመዘገቡ።

17አምላክ ሆይ፤ ለእኔ ያለህ ሐሳብ እንዴት ክቡር ነው!

ቍጥሩስ ምንኛ ብዙ ነው!

18ልቍጠራቸው ብል፣

ከአሸዋ ይልቅ ይበዙ ነበር።

ተኛሁም ነቃሁም፣

ገና ከአንተው ጋር ነኝ።

19አምላክ ሆይ፤ ክፉዎችን ብትገድላቸው ምናለበት!

ደም የተጠማችሁ ሰዎች ሆይ፤

ከእኔ ራቁ!

20ስለ አንተ በክፋት ይናገራሉና፤

ጠላቶችህም ስምህን በከንቱ ያነሣሉ።

21እግዚአብሔር ሆይ፤ የሚጠሉህን አልጠላምን?

በአንተ ላይ የሚነሡትንስ አልጸየፍምን?

22በፍጹም ጥላቻ ጠልቻቸዋለሁ፤

ባላጋራዎቼም ሆነዋል።

23እግዚአብሔር ሆይ፤ መርምረኝ፤ ልቤንም ዕወቅ፤

ፈትነኝ፤ ሐሳቤንም ዕወቅ፤

24የክፋት መንገድ በውስጤ ቢኖር እይ፤

በዘላለምም መንገድ ምራኝ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 139:1-24

139

1主よ。あなたは私の心の奥底まで探り、

どんなささいなことも見のがされません。

2私の立つのも座るのも、すべてご存じです。

遠くからでも、私の心をすべて読み取られます。

3あなたは、私の進む道もご存じで、

どこで休息をとるべきかも教えてくださいます。

どんなときも、私の居場所もご存じです。

4そして、口を開く前から、

私が何を言いたいかも見抜いておられます。

5あなたは私の前を行き、後ろからも来られます。

あなたは私に、祝福の御手を置いてくださいます。

6このようなことはあまりにも栄光にあふれ、

すばらしい話なので、

ほんとうだとは信じがたいほどです。

7あなたの視界から逃れることは決してできません。

身を隠すことも不可能です。

8天まで昇ろうと、あなたはそこにおられ、

死者の世界まで降りて行っても、

あなたはそこで待っておられるのです。

9朝風に乗って、地の果てまで飛んで行っても、

10あなたの力強い腕は、私を導き、支えてくださいます。

11私が暗闇にまぎれ込もうとしても、

夜は私を照らし出す光となるのです。

12暗闇も、神から隠れることはできません。

神から見れば、暗闇も光も同じようなものなのです。

13神は、精巧に私の体のすべての器官を造り、

母の胎内で組み立ててくださいました。

14こんなにも複雑かつ緻密に

仕上げてくださったことを感謝します。

想像することもできないくらい、すばらしいことです。

あなたのわざは驚くべきもので、

私にはとうてい、理解することはできません。

15だれも立ち入ることのできない場所で

私が組み立てられた時、あなたはそこにおられました。

16生まれる前から、まだ呼吸を始める前から、

あなたの目は私に注がれ、

私の生涯にわたるご計画も、

練り上げられていたのです。

17-18主よ。

あなたが私をかた時も忘れずにいてくださることは、

ほんとうにたいせつな事実です。

あなたは一日に、数えきれないほど何度も、

私のことを思い起こしてくださいます。

眠っているときも、朝までずっと、

私のことを考えていてくださるのです。

19悪者どもは必ず、主の御手にかかって滅びます。

血に飢えた者どもよ、すみやかに消え失せるがよい。

20彼らはあなたの御名を汚し、横柄な態度をとっています。

なんと愚かなことでしょう。

21主よ。あなたを憎む者どもを、

この私が憎まずにいられましょうか。

心を痛めずにいられましょうか。

22私は彼らを憎みます。

あなたの敵は私の敵だからです。

23ああ神よ。

私の心を探り、内面を調べ上げてください。

24あなたを悲しませるようなものがあるなら、

教えてください。

私が永遠のいのちへの道からそれないように

お導きください。