መዝሙር 140 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 140:1-13

መዝሙር 140

በክፉዎች ላይ የቀረበ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ከክፉ ሰዎች አድነኝ፤

ከዐመፀኞችም ሰዎች ጠብቀኝ፤

2እነርሱ በልባቸው ክፉ ነገር ያውጠነጥናሉ፤

በየዕለቱም ጦርነት ይጭራሉ።

3ምላሳቸውን እንደ እባብ ያሾላሉ፤

ከከንፈራቸውም በታች የእፉኝት መርዝ አለ። ሴላ

4እግዚአብሔር ሆይ፤ ከክፉዎች እጅ ጠብቀኝ፤

እግሮቼንም ለመጥለፍ ከሚያደቡ ዐመፀኞች ሰውረኝ።

5ትዕቢተኞች ወጥመድ በስውር አስቀመጡብኝ፤

የመረባቸውን ገመድ ዘረጉብኝ፤

በመንገዴም ላይ አሽክላ አኖሩ። ሴላ

6እግዚአብሔር ሆይ፤ “አንተ አምላኬ ነህ” እልሃለሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ የልመና ጩኸቴን ስማ።

7ብርቱ አዳኝ የሆንህ ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፤

በጦርነት ዕለት የራስ ቍር ሆንኸኝ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ የክፉዎች ምኞት አይፈጸም፤

በትዕቢትም እንዳይኵራሩ፣

ዕቅዳቸው አይሳካ። ሴላ

9ዙሪያዬን የከበቡኝ ሰዎች ራስ፣

የከንፈራቸው መዘዝ ይጠምጠምበት።

10የእሳት ፍም በላያቸው ይውረድ፤

ዳግመኛም እንዳይነሡ ወደ እሳት ይጣሉ፤

ማጥ ወዳለበት ጕድጓድ ይውደቁ።

11ምላሰኛ በምድሪቱ ጸንቶ አይኑር፤

ዐመፀኛውን ሰው ክፋት አሳድዶ ያጥፋው።

12እግዚአብሔር ለድኻ ፍትሕን እንደሚያስከብር፣

ለችግረኛውም ትክክለኛ ፍርድን እንደሚሰጥ ዐውቃለሁ።

13ጻድቃን በእውነት ስምህን ያመሰግናሉ፤

ቅኖችም በፊትህ ይኖራሉ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 140:1-13

140

1ああ主よ、私を悪者から救い出し、

乱暴者から守ってください。

2彼らは一日中、悪事を企み、

騒ぎを引き起こしています。

3彼らのことばは、毒蛇の牙のように人を刺すのです。

4彼らの手の届かない所に私を置き、

その暴力から守ってください。

彼らは危害を加えようと策略を練っています。

5彼らは傲慢で、

私を生け捕りにしようと罠をしかけました。

足をすくい、宙吊りにする輪なわを仕掛けます。

身動きがとれないように網をかけようと

待ち伏せています。

6-8ああ、私の救い主であり盾であられる主よ、

この祈りに耳を傾けてください。

悪者どもの思いどおりにはさせないでください。

彼らのすることがうまくいき、

彼らが傲慢になることがありませんように。

9その企みが、そのまま彼らの頭上に返りますように。

彼らが自分たちのしかけた罠で、

身を滅ぼしますように。

10赤々と燃える炭火を、その上に降らせてください。

また、火の中に、二度と上って来ることのできない

深い穴に、彼らを投げ込んでください。

11うそつきどもが、

この国で繁栄することがありませんように。

彼らをすみやかに罰してください。

12しかし主は、踏みにじられている人々を助け、

貧しい者の権利を守ってくださいます。

13神を信じて従う人は、

きっと感謝の声を上げるようになるでしょう。

神のおそばで暮らせる時が、必ずくるからです。