መዝሙር 135 – NASV & JCB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 135:1-21

መዝሙር 135

የምስጋና መዝሙር

135፥15-20 ተጓ ምብ – መዝ 115፥4-11

1ሃሌ ሉያ።135፥1 3 እና 21 ጭምር በአንዳንድ ትርጕሞች እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።

የእግዚአብሔርን ስም ወድሱ፤

እናንት የእግዚአብሔር አገልጋዮች ሆይ፤ አመስግኑት፤

2በእግዚአብሔር ቤት፣

በአምላካችን ቤት አደባባይ የምትቆሙ አመስግኑት።

3እግዚአብሔር ቸር ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤

መልካም ነውና፣ ለስሙ ዘምሩ፤

4እግዚአብሔር ያዕቆብን ለራሱ፣

እስራኤልንም ውድ ንብረቱ አድርጎ መርጧልና።

5እግዚአብሔር ታላቅ እንደ ሆነ፣

ጌታችንም ከአማልክት ሁሉ እንደሚበልጥ ዐውቃለሁና።

6በሰማይና በምድር፣

በባሕርና በጥልቅ ሁሉ ውስጥ፣

እግዚአብሔር ደስ ያሰኘውን ሁሉ ያደርጋል።

7እርሱ ደመናትን ከምድር ዳርቻ ያስነሣል፤

መብረቅ ከዝናብ ጋር እንዲወርድ ያደርጋል፤

ነፋሳትንም ከማከማቻው ያወጣል።

8በኵር ሆኖ በግብፅ የተወለደውን፣

ከሰው ጀምሮ እስከ እንስሳ ቀሠፈ።

9ግብፅ ሆይ፤ በፈርዖንና በአገልጋዮቹ ሁሉ ላይ፣

በመካከልሽ ታምራትንና ድንቅን ሰደደ።

10ብዙ ሕዝቦችን መታ፤

ኀያላን ነገሥታትንም ገደለ።

11የአሞራውያንን ንጉሥ ሴዎንን፣

የባሳንን ንጉሥ ዐግን፣

የከነዓንን ነገሥታት ሁሉ ገደለ፤

12ምድራቸውንም ርስት አድርጎ፣

ለሕዝቡ ርስት እንዲሆን ለእስራኤል ሰጠ።

13እግዚአብሔር ሆይ፤ ስምህ ዘላለማዊ ነው፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ መታሰቢያህም ከትውልድ እስከ ትውልድ ይኖራል።

14እግዚአብሔር ለሕዝቡ ይፈርዳልና፣

ለአገልጋዮቹም ይራራላቸዋል።

15የአሕዛብ ጣዖታት ከብርና ከወርቅ የተሠሩ፣

የሰው እጅ ያበጃቸው ናቸው።

16አፍ አላቸው፤ አይናገሩም፤

ዐይን አላቸው፤ አያዩም፤

17ጆሮ አላቸው፤ አይሰሙም፤

በአፋቸውም እስትንፋስ የለም።

18እነዚህን የሚያበጁ፣

የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ።

19የእስራኤል ቤት ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ፤

የአሮን ቤት ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ፤

20የሌዊ ቤት ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ፤

እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፤ እግዚአብሔርን ባርኩ።

21በኢየሩሳሌም የሚኖር እግዚአብሔር፣ ከጽዮን ይባረክ።

ሃሌ ሉያ።

Japanese Contemporary Bible

詩篇 135:1-21

135

1-2ハレルヤ。

主の民は、神殿の内庭に立って、ほめたたえなさい。

3恵み深い主のすばらしい御名をたたえて歌いなさい。

4主はイスラエルを、

ご自分のものとして選んでくださったのです。

5主の偉大さは、とてもほかの神々とは

比べものになりません。

6天も地も、深い海も、

主は思いどおりに治められます。

7地上にもやを立ちこめさせ、

雨をもたらすいなずまを光らせ、

その宝物倉から風を送り出されます。

8主はエジプト人に生まれた長男をみな、

家畜の初子もろとも滅ぼされました。

9エジプトの王や国民の目の前で、

大きな奇跡を見せられたのです。

10強い国々を滅ぼし、

負けを知らない王侯を殺されました。

11エモリ人の王シホン、バシャンの王オグ、

それにカナンの王たちを。

12主は彼らの土地を、ご自分の民イスラエルに、

永遠の贈り物としてお与えくださいました。

13ああ主よ。あなたの御名はいつまでもすたれず、

あらゆる時代の人々に知れ渡ります。

14主はご自分の民を弁護し、

仕える人々をあわれまれるからです。

15外国人は、人の手で作った金や銀の偶像を拝みます。

16口があってもしゃべれず、目があっても見えず、

17耳があっても聞こえす、

呼吸もしていない偶像を拝んでいるのです。

18偶像を作る者や、信仰する者も、同じく愚かです。

19イスラエルよ、主をほめたたえなさい。

アロンの家系の大祭司よ、ほめたたえなさい。

20レビの家系の祭司も、

主を信じて従う人々も、

主をほめたたえなさい。

21エルサレムの住民よ、ほめたたえなさい。

エルサレムは主の御住まいではありませんか。