መዝሙር 129
በጽዮን ጠላቶች ላይ የቀረበ ጸሎት
መዝሙረ መዓርግ።
1እስራኤል እንዲህ ይበል፦
“ከልጅነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ አስጨነቁኝ፤
2በርግጥ ከልጅነቴ ጀምሮ ብዙ ጊዜ አስጨነቁኝ፤
ዳሩ ግን ድል አላደረጉኝም።
3ዐራሾች ጀርባዬን ዐረሱት፤
ትልማቸውንም አስረዘሙት።”
4እግዚአብሔር ግን ጻድቅ ነው፤
የክፉዎችን ገመድ በጣጥሶ ጣለው።
5ጽዮንን የሚጠሉ ሁሉ፣
ዐፍረው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።
6ገና ከመብቀሉ እንደሚደርቅ፣
በጣራ ላይ እንደ በቀለ ሣር ይሁኑ፤
7ደግሞም ለዐጫጅ እጁን፣
ለነዶ ሰብሳቢ ዕቅፉን እንደማይሞላ ይሁኑ።
8መንገድ ዐላፊዎችም፣
“የእግዚአብሔር በረከት በእናንተ ላይ ይሁን፤
በእግዚአብሔር ስም እንባርካችኋለን” አይበሉ።
الْمَزْمُورُ الْمِئَةُ وَالتَّاسِعُ وَالْعِشْرُونَ
تَرْنِيمَةُ الْمَصَاعِدِ
1مَا أَكْثَرَ مَا ضَايَقُونِي فِي حَدَاثَتِي يَقُولُ إِسْرَائِيلُ. 2مَا أَكْثَرَ مَا ضَايَقُونِي فِي حَدَاثَتِي، لَكِنَّهُمْ لَمْ يَتَغَلَّبُوا عَلَيَّ. 3جَرَحُوا ظَهْرِي جُرُوحاً عَمِيقَةً، فَصَارَ كَالأَتْلامِ (خُطُوطِ الْمِحْرَاثِ) الطَّوِيلَةِ فِي حَقْلٍ مَحْرُوثٍ. 4الرَّبُّ عَادِلٌ، كَسَرَ أَغْلالَ عُبُودِيَّةِ الأَشْرَارِ. 5فَلْيَخْزَ وَلْيُدْبِرْ جَمِيعُ مُبْغِضِي صِهْيَوْنَ. 6لِيَكُونُوا كَالْعُشْبِ النَّابِتِ عَلَى السُّطُوحِ، الَّذِي يَجِفُّ قَبْلَ أَنْ يَنْمُوَ، 7فَلَا يَمْلأُ الْحَاصِدُ مِنْهُ يَدَهُ، وَلَا الْحَازِمُ حِضْنَهُ. 8وَلَا يَقُولُ عَابِرُو السَّبِيلِ لَهُمْ: «لِتَكُنْ عَلَيْكُمْ بَرَكَةُ الرَّبِّ: نُبَارِكُكُمْ بِاسْمِ الرَّبِّ».