መዝሙር 11 – NASV & BPH

New Amharic Standard Version

መዝሙር 11:1-7

መዝሙር 11

የጻድቃን ትምክሕት

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1በእግዚአብሔር ታምኛለሁ፤

ታዲያ ነፍሴን፣ “እንደ ወፍ ወደ ተራራ ብረሪ”

ለምን ትሏታላችሁ?

2ደግሞም ለምን እንዲህ ትሉኛላችሁ?

“ክፉዎች፣ እነሆ፤ ቀስታቸውን ገትረዋል፤

የቅኑን ሰው ልብ በጨለማ ለመንደፍ፣

ፍላጻቸውን በአውታሩ ላይ ደግነዋል።

3መሠረቱ ከተናደ፣

ጻድቅ ምን ማድረግ ይችላል?”11፥3 ወይም ጻድቁ ምን እያደረገ ነው?

4እግዚአብሔር በተቀደሰ መቅደሱ አለ፤

የእግዚአብሔር ዙፋን በሰማይ ነው።

ዐይኖቹ ሰዎችን ይመለከታሉ፤

ቅንድቦቹም የሰው ልጆችን ይመረምራሉ።

5እግዚአብሔር ጻድቁንና ኀጥኡን ይመረምራል፤11፥5 ወይም ጻድቁ እግዚአብሔር ኀጥኡን ይመረምራል

ዐመፃን የሚወድዱትን ግን፣

ነፍሱ ትጠላቸዋለች።

6እርሱ በክፉዎች ላይ የእሳት ፍምና ዲን ያዘንባል፤

የጽዋቸውም ዕጣ ፈንታ፣

የሚለበልብ ዐውሎ ነፋስ ነው።

7እግዚአብሔር ጻድቅ ነውና፤

የጽድቅ ሥራም ይወድዳል፤

ቅኖችም ፊቱን ያያሉ።

Bibelen på hverdagsdansk

Salmernes Bog 11:1-7

Tilflugt hos Herren

1Til korlederen: En sang af David.

Jeg stoler på Herren og søger hans hjælp.

Hvorfor siger I: „Flygt op i bjergene som en fugl,

2for de gudløse har spændt deres bue og lagt pilen til rette.

De gemmer sig i mørket for at ramme de retskafne.

3Hvad kan en gudfrygtig gøre, når al lov og ret er borte?”

4Herren sidder i sit hellige tempel.

Han regerer fra sin trone i Himlen.

Han overvåger hvert menneske på jorden.

5Han gennemskuer både de gode og de gudløse.

Han hader dem, som elsker vold.

6Han lader gloende kul regne ned over de onde,

straffer dem med rygende svovl og en brændende vind.

7Herren er god og elsker dem, der adlyder ham,

de, som gør det gode, skal se hans ansigt.