መሳፍንት 7 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 7:1-25

ጌዴዎን ምድያማውያንን ድል አደረገ

1ይሩበኣል የተባለው ጌዴዎን፣ ከእርሱም ጋር የነበሩት ሰዎች ሁሉ በጧት ተነሥተው በሐሮድ ምንጭ አጠገብ ሰፈሩ። የምድያማውያንም ሰፈር እስራኤላውያን ከሰፈሩበት በስተ ሰሜን በኩል፣ በሞሬ ኰረብታ አጠገብ በሸለቆው ውስጥ ነበር። 2እግዚአብሔር ጌዴዎንን እንዲህ አለው፤ “ምድያማውያንን በእጃቸው አሳልፌ እንዳልሰጥ አብረውህ ያሉት ሰዎች በጣም ብዙ ናቸው፤ እስራኤላውያን የገዛ ኀይላቸው እንዳዳናቸው በመቍጠር እንዳይታበዩብኝ፣ 3‘ማንም የፈራ ቢኖር የገለዓድን ተራራ ትቶ ወደ መጣበት ይመለስ’ ብለህ ለሕዝቡ ዐውጅ።” ስለዚህ ሃያ ሁለቱ ሺሕ ሲመለሱ ዐሥሩ ሺሕ ብቻ ቀሩ።

4እግዚአብሔር ጌዴዎንን እንዲህ አለው፤ “አሁንም ሰዎቹ ብዙ ናቸው፤ ወደ ወንዝ ይዘሃቸው ውረድ፤ በዚያም እለይልሃለሁ። ‘ይህ ከአንተ ጋር ይሂድ’ የምለው፣ ከአንተ ጋር ይሄዳል፤ ነገር ግን፣ ‘ይህ ከአንተ ጋር አይሂድ’ የምለው፣ ከአንተ ጋር አይሄድም።”

5ስለዚህ ጌዴዎን ሰዎቹን ወደ ወንዝ ይዟቸው ወረደ፤ እዚያም እግዚአብሔር፤ “ውሻ በምላሱ እየጨለፈ እንደሚጠጣ ሁሉ፣ በምላሳቸው የሚጠጡትን፣ በጕልበታቸው ተንበርክከው ከሚጠጡት ለይ” አለው። 6ሦስት መቶ ሰዎች ውሃውን በእጃቸው እያፈሱ ጠጡ፤ የቀሩት ሁሉ ግን ለመጠጣት በጕልበታቸው ተንበረከኩ።

7እግዚአብሔርም ጌዴዎንን፣ “ውሃውን በእጃቸው እያፈሱ በጠጡት ሦስት መቶ ሰዎች አድናችኋለሁ፤ ምድያማውያንንም በእጃችሁ አሳልፌ እሰጣችኋለሁ፤ የቀሩት በሙሉ ወደየመጡበት ይመለሱ” አለው። 8ጌዴዎንም የቀሩትን እስራኤላውያን በሙሉ ወደ የድንኳናቸው እንዲመለሱ አደረገ፤ ሦስት መቶውን ግን አስቀራቸው፤ እነርሱም የሚመለሱትን ሰዎች ስንቅና መለከት ወሰዱ።

በዚህ ጊዜ የምድያማውያኑ ሰፈር ከእነርሱ በታች በሸለቋማው ውስጥ ነበር። 9በዚያች ሌሊት እግዚአብሔር ጌዴዎንን እንዲህ አለው፤ “ተነሥ፤ በሰፈሩም ላይ ውረድ፤ በእጅህ አሳልፌ ሰጥቼሃለሁና። 10አደጋ ለመጣል የምትፈራ ከሆነ ግን፣ ፉራ ከተባለው አገልጋይህ ጋር ወደ ሰፈሩ ውረድ፤ 11የሚሉትንም አድምጥ፤ ከዚያ በኋላ በሰፈሩ ላይ አደጋ ለመጣል ድፍረት ታገኛለህ።” ስለዚህም ጌዴዎን አገልጋዩን ፉራን አስከትሎ እስከ ሰፈሩ ዳርቻ ወረደ። 12ብዛታቸው እንደ አንበጣ መንጋ የሆነ ምድያማውያን፣ አማሌቃውያንና ሌሎችም የምሥራቅ ሕዝቦች በሸለቆው ውስጥ ሰፍረው ነበር፤ የግመሎቻቸውም ብዛት በባሕር ዳርቻ እንዳለ አሸዋ ስፍር ቍጥር አልነበረውም።

13አንድ ሰው ያየውን ሕልም ለጓደኛው በሚነግርበት ጊዜ ጌዴዎን እዚያ ደረሰ። ያም ሰው፣ “በሕልሜ ክብ የሆነ አንድ የገብስ ቂጣ ከላይ ተንከባሎ በምድያማውያን ሰፈር ላይ ሲወርድ፣ ድንኳኑንም ሲመታው ከአመታቱም ኀይለኛነት የተነሣ ድንኳኑ ተገልብጦ ሲፈራርስ አየሁ” በማለት ይነግረው ነበር።

14ጓደኛውም መልሶ፣ “ይህ የእስራኤላዊው የኢዮአስ ልጅ የጌዴዎን ሰይፍ እንጂ ሌላ ነገር ሊሆን አይችልም፤ እነሆ፤ እግዚአብሔር ምድያማውያንንና ሰፈሩን በሙሉ በእጁ አሳልፎ ሰጥቶታልና” አለው።

15ጌዴዎንም ሕልሙንና ፍቺውን በሰማ ጊዜ ለእግዚአብሔር ሰገደ፤ ከዚያም ወደ እስራኤላውያን ሰፈር ወጥቶ፣ “እግዚአብሔር የምድያማውያንን ሰፈር በእጃችሁ አሳልፎ ሰጥቷልና ተነሡ” አላቸው። 16ሦስቱን መቶ ሰዎች በሦስት ቡድን ከፍሎ፣ እያንዳንዱን ሰው ቀንደ መለከትና በውስጡ ችቦ ያለበት ባዶ ማሰሮ በእጁ እንዲይዝ አደረገ።

17ጌዴዎንም እንዲህ አላቸው፤ “እኔን ተመልከቱ፤ የማደርገውንም አድርጉ፤ በሰፈሩ ዳርቻ ስደርስ እኔ የማደርገውን አይታችሁ ልክ እንደዚያው አድርጉ። 18እኔና አብረውኝ ያሉት ሁሉ ቀንደ መለከቶቻችንን በምንነፋበት ጊዜ እናንተም በሰፈሩ ዙሪያ ሁሉ ቀንደ መለከቶቻችሁን እየነፋችሁ፣ ‘ለእግዚአብሔርና ለጌዴዎን’ ብላችሁ ጩኹ።”

19ዘቦቹ ተቀያይረው የእኩለ ሌሊቱን ጥበቃ በጀመሩበት ጊዜ፣ ጌዴዎንና አብረውት የነበሩት መቶ ሰዎች በሰፈሩ ዳርቻ ደረሱ፤ እነርሱም ቀንደ መለከቶቻቸውን ነፉ፤ የያዟቸውንም ማሰሮች ሰበሩ። 20በሦስት ቡድን የተከፈሉት ሰዎች ቀንደ መለከቶቻቸውን ነፉ፤ ማሰሮቻቸውንም ሰበሩ፤ ችቦዎቻቸውን በግራ እጆቻቸው፣ የሚነፏቸውንም ቀንደ መለከቶች በቀኝ እጆቻቸው ይዘው፣ “የእግዚአብሔርና የጌዴዎን ሰይፍ” በማለት ጮኹ። 21እያንዳንዱ ሰው በሰፈሩ ዙሪያ የተመደበበትን ቦታ እንደ ያዘም ምድያማውያኑ እየጮኹ ሸሹ።

22የሦስት መቶው ቀንደ መለከት ድምፅ እንደ ተሰማም እግዚአብሔር በሰፈሩ ውስጥ ያለው ሰው አንዱ በሌላው ላይ ሰይፉን እንዲመዝበት አደረገ፤ ሰራዊቱ በጽሬራ አቅጣጫ ወደ ቤት ሺጣ፣ ከዚያም ዐልፈው በጠባት አጠገብ እስካለው እስከ አቤላሞሖላ ድንበር ድረስ ሸሽተው ሄዱ። 23በንፍታሌም፣ በአሴርና በመላው የምናሴ ምድር የሚገኙ እስራኤላውያን ተጠርተው ወጡ፤ ምድያማውያንንም አሳደዱ። 24ጌዴዎንም በኤፍሬም ኰረብታማ አገር ለሚኖሩት ሁሉ፣ “በምድያማውያን ላይ ውረዱ፤ እስከ ቤትባራ ድረስ ያለውንም የዮርዳኖስ ወንዝ ቀድማችሁ ያዙ” አላቸው።

ስለዚህ የኤፍሬም ሰዎች ሁሉ ተጠርተው ወጡ፤ እስከ ቤትባራ ድረስ ያለውንም የዮርዳኖስን ወንዝ ያዙ። 25እንዲሁም ሔሬብና ዜብ የተባሉትን ሁለቱን የምድያም መሪዎች ያዙ። ሔሬብን በሔሬብ ዐለት አጠገብ፣ ዜብን ደግሞ በዜብ የወይን መጭመቂያ ላይ ገደሏቸው፤ ምድያማውያንንም አሳደዱ፤ የሔሬብንና የዜብን ራስ ቈርጠው ጌዴዎን ወዳለበት ወደ ዮርዳኖስ ይዘው መጡ።

Persian Contemporary Bible

داوران 7:1-25

جدعون مديانی‌ها را شكست می‌دهد

1جدعون با سپاهش صبح زود حركت كرد و تا چشمهٔ حرود پيش رفت و در آنجا اردو زد. مديانی‌ها نيز در سمت شمالی آنها در درهٔ كوه موره اردو زده بودند.

2خداوند به جدعون فرمود: «عدهٔ شما زياد است! نمی‌خواهم همهٔ اين افراد با مديانی‌ها بجنگند، مبادا قوم اسرائيل مغرور شده، بگويند: اين ما بوديم كه دشمن را شكست داديم! 3پس به افراد خود بگو: هر كه می‌ترسد به خانه‌اش بازگردد.» بنابراين بيست و دو هزار نفر برگشتند و فقط ده هزار نفر ماندند تا بجنگند. 4اما خداوند به جدعون فرمود: «هنوز هم عده زياد است! آنها را نزد چشمه بياور تا به تو نشان دهم كه چه كسانی بايد با تو بيايند و چه كسانی بايد برگردند.»

5‏-6پس جدعون آنها را به كنار چشمه برد. در آنجا خداوند به او گفت: «آنها را از نحوهٔ آب خوردنشان به دو گروه تقسيم كن. افرادی را كه با كفِ دست، آب را جلو دهان خود آوردند و آن را مثل سگ می‌نوشند از كسانی كه زانو می‌زنند و دهان خود را در آب می‌گذارند، جدا ساز.» تعداد افرادی كه با دست آب نوشيدند سيصد نفر بود.

7آنگاه خداوند به جدعون فرمود: «من بوسيلهٔ اين سيصد نفر، مديانی‌ها را شكست خواهم داد و شما را از دستشان خواهم رهانيد. پس بقيه را به خانه‌هايشان بفرست.»

8‏-9جدعون كوزه‌ها و شيپورهای آنها را جمع‌آوری كرد و ايشان را به خانه‌هايشان فرستاد و تنها سيصد نفر برگزيده را پيش خود نگاه داشت.

شب هنگام در حالی که مدیانیان در درهٔ پايين اردو زده بودند، خداوند به جدعون فرمود: «برخيز و به اردوی دشمن حمله كن زيرا آنها را به دست تو تسليم كرده‌ام. 10اما اگر می‌ترسی اول با نوكر خود فوره مخفيانه به اردوگاه آنها برو. 11در آنجا به سخنانی كه ايشان می‌گويند گوش بده. وقتی سخنان آنها را بشنوی جرأت يافته، به ايشان حمله خواهی كرد!» پس جدعون فوره را با خود برداشت و مخفيانه به اردوگاه دشمن نزديک شد. 12‏-13مدیانیان، عماليقی‌ها و ساير قبايل همسايه مانند مور و ملخ در وادی جمع شده بودند. شترهايشان مثل ريگ بيابان بی‌شمار بود. جدعون به كنار چادری خزيد. در اين موقع در داخل آن چادر مردی بيدار شده، خوابی را كه ديده بود برای رفيقش چنين تعريف كرد: «در خواب ديدم كه يک قرص نان جوين به ميان اردوی ما غلطيد و چنان به خيمه‌ای برخورد نمود كه آن را واژگون كرده، بر زمين پهن نمود.» 14رفيق او گفت: «تعبير خواب تو اين است كه خدا ما را به دست جدعون پسر يوآش اسرائيلی تسليم می‌كند و جدعون همهٔ مدیانیان و نيروهای متحدش را از دم شمشير خواهد گذراند.»

15جدعون چون اين خواب و تعبيرش را شنيد خدا را شكر كرد. سپس به اردوگاه خود بازگشت و فرياد زد: «برخيزيد! زيرا خداوند سپاه مديان را به دست شما تسليم می‌كند!»

16جدعون آن سيصد نفر را به سه دسته تقسيم كرد و به هر يک از افراد يک شيپور و يک كوزهٔ سفالی كه مشعلی در آن قرار داشت، داد. 17بعد نقشهٔ خود را چنين شرح داد: «وقتی به كنار اردو رسيديم به من نگاه كنيد و هر كاری كه من می‌كنم شما نيز بكنيد. 18به محض اينكه من و همراهانم شيپورها را بنوازيم، شما هم در اطراف اردو شيپورهای خود را بنوازيد و با صدای بلند فرياد بزنيد: ما برای خداوند و جدعون می‌جنگيم!»

19‏-20نصف شب، بعد از تعويض نگهبانان، جدعون به همراه صد نفر به كنار اردوی مديان رسيد. ناگهان آنها شيپورها را نواختند و كوزه‌ها را شكستند. در همين وقت دويست نفر ديگر نيز چنين كردند. در حالی كه شيپورها را به دست راست گرفته، می‌نواختند و مشعلهای فروزان را در دست چپ داشتند همه فرياد زدند: «ما برای خداوند و جدعون می‌جنگيم!» 21سپس هر يک در جای خود در اطراف اردوگاه ايستادند در حالی که افراد دشمن فريادكنان می‌گريختند. 22زيرا وقتی صدای شيپورها برخاست خداوند سربازان دشمن را در سراسر اردو به جان هم انداخت. آنها تا بيت‌شطه نزديک صريرت و تا سرحد آبل محوله، نزديک طبات گريختند.

23آنگاه سپاهيان نفتالی، اشير و منسی سپاهيان فراری مديان را تعقيب كردند. 24جدعون برای ساكنان سراسر كوهستان افرايم پيغام فرستاد كه گذرگاههای رود اردن را تا بيت‌باره ببندند و نگذارند مدیانیان از رودخانه عبور كرده، فرار كنند. پس تمام مردان افرايم جمع شده، چنين كردند. 25آنها غراب و ذئب دو سردار مديانی را گرفتند و غراب را بر صخره‌ای كه اكنون به نام او معروف است و ذئب را در چرخشتی كه به اسم او ناميده می‌شود كشتند. سپس به تعقيب مديانی‌ها ادامه داده، سرهای غراب و ذئب را به آن طرف اردن نزد جدعون آوردند.