ሕዝቅኤል 47 – NASV & NIV

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 47:1-23

ከቤተ መቅደሱ ተነሥቶ የሚፈውስ ወንዝ

1ከዚያም ያ ሰው ወደ ቤተ መቅደሱ መግቢያ መልሶ አመጣኝ፤ ከቤተ መቅደሱ መድረክ ሥር ውሃ እየወጣ፣ ወደ ምሥራቅ ይፈስስ ነበር፤ ቤተ መቅደሱ ለምሥራቅ ትይዩ ነበርና። ውሃው ከቤተ መቅደሱ በስተ ደቡብ በኩል፣ በመሠዊያው ደቡብ በኩል፣ ሥር ሥሩን ይወርዳል። 2ከዚያም በሰሜኑ በር በማውጣት በውጭ አዙሮ በምሥራቅ አቅጣጫ ወዳለው የውጭ በር መራኝ፤ ውሃውም በደቡብ በኩል ይፈስስ ነበር። 3ያም ሰው የመለኪያውን ገመድ በእጁ ይዞ ወደ ምሥራቅ በመሄድ፣ አንድ ሺሕ ክንድ ለካ፤ ከዚያም እስከ ቍርጭምጭሚት በሚደርሰው ውሃ ውስጥ መራኝ፤ 4ቀጥሎም አንድ ሺሕ ክንድ ለካ፤ እስከ ጕልበት ወደሚደርስም ውሃ መራኝ፤ ከዚያም ሌላ አንድ ሺሕ ክንድ ለካ፤ እስከ ወገብ ወደሚደርስም ውሃ መራኝ። 5እንደ ገናም አንድ ሺሕ ክንድ ለካ፤ አሁን ግን ልሻገረው የማልችል ወንዝ ሆነ፤ ምክንያቱም ውሃው ስለ ሞላና ጥልቅ ስለ ነበረ፣ በዋና ካልሆነ በስተቀር በእግር ሊሻገሩት የማይቻል ነበረ። 6እርሱም፣ “የሰው ልጅ ሆይ፤ ይህን ታየዋለህን?” ሲል ጠየቀኝ።

ከዚያም መልሶ ወደ ወንዙ ዳር መራኝ፤ 7እዚያም በደረስሁ ጊዜ፣ በወንዙ ግራና ቀኝ ብዙ ዛፍ አየሁ። 8እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “ይህ ውሃ ወደ ምሥራቅ ምድር ይፈስሳል፤ ወደ ባሕሩ ወደሚገባበት ወደ ዓረባ47፥8 ወይም ወደ ዮርዳኖስ ሸለቆ ይወርዳል፤ ወደ ባሕሩም47፥8 ሙት ባሕርን ያመለክታል። ሲፈስስ፣ በዚያ የነበረው ውሃ ንጹሕ ይሆናል። 9ወንዙ በሚፈስስበት ስፍራ ሁሉ ብዙ ሕያዋን ፍጡራን ይኖራሉ። ይህ ውሃ በዚያ ስለሚፈስስና ጨውማ የሆነውን ውሃ ንጹሕ ስለሚያደርገው፣ ዓሣ በብዛት ይኖራል፤ ስለዚህ ወንዙ በሚፈስስበት ስፍራ ሁሉ ማንኛውም ነገር በሕይወት ይኖራል። 10ዓሣ አጥማጆች በወንዙ ዳር ይቆማሉ፤ ከዓይንጋዲ እስከ ዓይንኤግላይም ድረስ ያለው ቦታ መረብ መዘርጊያ ይሆናል፤ ዓሣውም እንደ ታላቁ ባሕር47፥10 ሜድትራኒያንን ያመለክታል፤ እንዲሁም 19 እና 20 ዓሣ፣ የተለያየ ዐይነት ይሆናል። 11ነገር ግን ረግረጉና ዕቋሪው ውሃ ንጹሕ አይሆንም፤ ጨው እንደ ሆነ ይቀራል። 12በወንዙም ዳርና ዳር፣ ፍሬ የሚያፈሩ የዛፍ ዐይነቶች ሁሉ ይበቅላሉ፤ ቅጠላቸው አይደርቅም፤ ፍሬ አልባም አይሆኑም። ከመቅደሱ የሚወጣው ውሃ ስለሚፈስላቸው በየወሩ ያፈራሉ፤ ፍሬያቸው ለምግብ፣ ቅጠላቸውም ለፈውስ ይሆናል።”

የምድሪቱ ወሰን

13ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “ምድሪቱን ርስት አድርገህ ለዐሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገድ የምታከፋፍሉባቸው ወሰኖች እነዚህ ናቸው፤ ዮሴፍ ሁለት ዕጣ ይኑረው። 14እኩል አድርጋችሁ ከፋፍሉት፤ ለቀድሞ አባቶቻችሁ እሰጣቸው ዘንድ በተዘረጋች እጅ ስለ ማልሁ፣ ምድሪቱ ርስታችሁ ትሆናለች።

15“የምድሪቱ ወሰን ይህ ነው፤

“በሰሜን በኩል ከታላቁ ባሕር አንሥቶ በሔትሎን መንገድ በሐማት መተላለፊያ አድርጎ እስከ ጽዳድ ይደርሳል፤ 16ከዚያም ቤሮታን፣47፥15-16 ሰብዐ ሊቃናትንና ሕዝ 48፥1 ይመ፤ ዕብራይስጡ ግን ወደ ዘዳድ የሚወስደው መንገድ፣ 16 ሐማት ቤሮታን… ይላል። በደማስቆና በሐማት ወሰን መካከል ያለውን ሲብራይምን ዐልፎ፣ በሐውራን ወሰን ላይ እስካለው እስከ ሐጸርሃቲኮን ይዘልቃል። 17ወሰኑ ከባሕሩ በመነሣት፣ በሰሜኑ የደማስቆ ድንበር አድርጎ፣ የሐማትንም ዳርቻ ወደ ሰሜን ትቶ እስከ ሐጸርዔናን47፥17 በዕብራይስጥ ዔኖን የዔናን አማራጭ ትርጕም ነው። ይዘልቃል።

18በምሥራቅ በኩል ወሰኑ በሐውራንና በደማስቆ መካከል፣ በገለዓድና በእስራኤል ምድር መካከል ዮርዳኖስ ይሆናል፤ የምሥራቁ ድንበር እስከ ምሥራቁ ባሕር ይወርድና እስከ ታማር47፥18 ሰብዐ ሊቃናትና ሱርስት እንዲሁ ሲሆኑ ዕብራይስጡ ግን እስራኤል፤ ባሕሩን በምሥራቅ በኩል ትለካለህ፤ ይላል። ይዘልቃል፤ ይህም የምሥራቁ ወሰን ይሆናል።

19በደቡብ በኩል ወሰኑ ከታማር ይነሣና እስከ ሜሪባ ቃዴስ ውሃ ይደርሳል፤ ከዚያም የግብፅን ደረቅ ወንዝ ተከትሎ እስከ ታላቁ ባሕር ይዘልቃል፤ ይህ የደቡቡ ወሰን ነው።

20በምዕራቡ በኩል ወሰኑ ከሐማት መግቢያ ፊት ለፊት እስካለው ቦታ ድረስ ታላቁ ባሕር ይሆናል፤ ይህም የምዕራቡ ወሰን ይሆናል።

21“እነሆ፤ ይህችን ምድር በእስራኤል ነገድ ቍጥር ልክ ትከፋፈላላችሁ፤ 22ለራሳችሁ፣ በመካከላችሁ ለሚኖሩት ልጆች ላሏቸው መጻተኞች ርስት አድርጋችሁ መድቡ፤ እነርሱንም እንደ እስራኤል ተወላጆች ቍጠሯቸው፤ እንደ እናንተ ከእስራኤል ነገዶች ርስት ይመደብላቸው። 23መጻተኛ በማንኛውም ነገድ መካከል ቢቀመጥ፣ በዚያ ርስቱን ስጡት፤” ይላል ጌታ እግዚአብሔር

New International Version

Ezekiel 47:1-23

The River From the Temple

1The man brought me back to the entrance to the temple, and I saw water coming out from under the threshold of the temple toward the east (for the temple faced east). The water was coming down from under the south side of the temple, south of the altar. 2He then brought me out through the north gate and led me around the outside to the outer gate facing east, and the water was trickling from the south side.

3As the man went eastward with a measuring line in his hand, he measured off a thousand cubits47:3 That is, about 1,700 feet or about 530 meters and then led me through water that was ankle-deep. 4He measured off another thousand cubits and led me through water that was knee-deep. He measured off another thousand and led me through water that was up to the waist. 5He measured off another thousand, but now it was a river that I could not cross, because the water had risen and was deep enough to swim in—a river that no one could cross. 6He asked me, “Son of man, do you see this?”

Then he led me back to the bank of the river. 7When I arrived there, I saw a great number of trees on each side of the river. 8He said to me, “This water flows toward the eastern region and goes down into the Arabah,47:8 Or the Jordan Valley where it enters the Dead Sea. When it empties into the sea, the salty water there becomes fresh. 9Swarms of living creatures will live wherever the river flows. There will be large numbers of fish, because this water flows there and makes the salt water fresh; so where the river flows everything will live. 10Fishermen will stand along the shore; from En Gedi to En Eglaim there will be places for spreading nets. The fish will be of many kinds—like the fish of the Mediterranean Sea. 11But the swamps and marshes will not become fresh; they will be left for salt. 12Fruit trees of all kinds will grow on both banks of the river. Their leaves will not wither, nor will their fruit fail. Every month they will bear fruit, because the water from the sanctuary flows to them. Their fruit will serve for food and their leaves for healing.”

The Boundaries of the Land

13This is what the Sovereign Lord says: “These are the boundaries of the land that you will divide among the twelve tribes of Israel as their inheritance, with two portions for Joseph. 14You are to divide it equally among them. Because I swore with uplifted hand to give it to your ancestors, this land will become your inheritance.

15“This is to be the boundary of the land:

“On the north side it will run from the Mediterranean Sea by the Hethlon road past Lebo Hamath to Zedad, 16Berothah47:15,16 See Septuagint and 48:1; Hebrew road to go into Zedad, 16 Hamath, Berothah. and Sibraim (which lies on the border between Damascus and Hamath), as far as Hazer Hattikon, which is on the border of Hauran. 17The boundary will extend from the sea to Hazar Enan,47:17 Hebrew Enon, a variant of Enan along the northern border of Damascus, with the border of Hamath to the north. This will be the northern boundary.

18“On the east side the boundary will run between Hauran and Damascus, along the Jordan between Gilead and the land of Israel, to the Dead Sea and as far as Tamar.47:18 See Syriac; Hebrew Israel. You will measure to the Dead Sea. This will be the eastern boundary.

19“On the south side it will run from Tamar as far as the waters of Meribah Kadesh, then along the Wadi of Egypt to the Mediterranean Sea. This will be the southern boundary.

20“On the west side, the Mediterranean Sea will be the boundary to a point opposite Lebo Hamath. This will be the western boundary.

21“You are to distribute this land among yourselves according to the tribes of Israel. 22You are to allot it as an inheritance for yourselves and for the foreigners residing among you and who have children. You are to consider them as native-born Israelites; along with you they are to be allotted an inheritance among the tribes of Israel. 23In whatever tribe a foreigner resides, there you are to give them their inheritance,” declares the Sovereign Lord.