ሐዋርያት ሥራ 7 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ሐዋርያት ሥራ 7:1-60

እስጢፋኖስ በሸንጎው ፊት ያደረገው ንግግር

1ሊቀ ካህናቱም፣ “ይህ የቀረበብህ ክስ እውነት ነውን?” አለው።

2እስጢፋኖስም እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ወንድሞችና አባቶች ሆይ፤ አድምጡኝ! አባታችን አብርሃም ወደ ካራን ከመምጣቱ በፊት፣ ገና በመስጴጦምያ ሳለ፣ የክብር አምላክ ተገልጦለት፣ 3‘ከአገርህና ከወገንህ ተለይተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ሂድ’ አለው።

4“እርሱም ከከለዳውያን ምድር ወጥቶ በካራን ተቀመጠ። ከአባቱም ሞት በኋላ፣ አሁን እናንተ ወደምትኖሩበት ወደዚህ አገር አመጣው። 5በዚህም ስፍራ አንዲት ጫማ ታህል እንኳ ርስት አልሰጠውም፤ ነገር ግን በዚያን ጊዜ ምንም ልጅ ሳይኖረው፣ እርሱና ከእርሱም በኋላ ዘሩ ምድሪቱን እንደሚወርሱ እግዚአብሔር ቃል ገባለት። 6ደግሞም እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ ተናገረው፤ ‘ዘርህ በባዕድ አገር መጻተኛ ይሆናል፤ አራት መቶ ዓመትም በባርነት ቀንበር ሥር ይማቅቃል። 7ሆኖም በባርነት የሚገዛቸውን ሕዝብ እኔ ደግሞ እቀጣዋለሁ። ከዚያም አገር ወጥተው በዚህች ስፍራ ያመልኩኛል።’ 8ከዚያም የግዝረትን ኪዳን ሰጠው፤ አብርሃምም ይስሐቅን ወለደ፤ በስምንተኛውም ቀን ገረዘው። ይስሐቅም ያዕቆብን ወለደ፤ ያዕቆብም ዐሥራ ሁለቱን የነገድ አባቶች ወለደ።

9“የነገድ አባቶችም በዮሴፍ ቀንተው በባርነት ወደ ግብፅ ሸጡት፤ እግዚአብሔር ግን ከእርሱ ጋር ስለ ነበር፣ 10ከመከራው ሁሉ አወጣው፤ በግብፅም ንጉሥ በፈርዖን ፊት ሞገስና ጥበብን አጐናጸፈው፤ ፈርዖንም በግብፅና በቤተ መንግሥቱ ሁሉ ላይ ኀላፊ አድርጎ ሾመው።

11“በዚያ ጊዜም በግብፅና በከነዓን አገር ሁሉ ታላቅ መከራን ያስከተለ ራብ መጣ፤ አባቶቻችንም የሚበሉትን ዐጡ። 12ያዕቆብም እህል በግብፅ መኖሩን በሰማ ጊዜ፣ አባቶቻችንን ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ግብፅ ላካቸው፤ 13ለሁለተኛ ጊዜ ሲሄዱ ደግሞ ዮሴፍ ማንነቱን ለወንድሞቹ ገለጠ፤ ፈርዖንም ስለ ዮሴፍ ዘመዶች ተረዳ። 14ከዚህ በኋላ፣ ዮሴፍ ልኮ አባቱን ያዕቆብንና ሰባ አምስት ነፍስ የሚሆኑ ቤተ ዘመዶቹን በሙሉ አስመጣ። 15ያዕቆብ ወደ ግብፅ ወረደ፤ እርሱም አባቶቻችንም በዚያ ሞቱ። 16አስከሬናቸውም ወደ ሴኬም ተወስዶ፣ አብርሃም ከዔሞር ልጆች ላይ በጥሬ ብር በገዛው መቃብር ተቀበረ።

17“እግዚአብሔር ለአብርሃም የገባው ቃል የሚፈጸምበት ጊዜ ሲቃረብም፣ በግብፅ የነበረው የሕዝባችን ቍጥር እየበዛ ሄደ። 18ከዚያ በኋላ ዮሴፍን የማያውቅ ሌላ ንጉሥ በግብፅ ነገሠ። 19እርሱም ሕዝባችንን በተንኰሉ አስጨነቀ፤ ገና የተወለዱ ሕፃናታቸውም ይሞቱ ዘንድ ወደ ውጭ አውጥተው እንዲጥሏቸው አስገደዳቸው።

20“በዚህ ጊዜ ሙሴ ተወለደ፤ እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ሞገስን ያገኘ ውብ ሕፃን7፥20 ወይም ተራ ልጅ አልነበረም ነበር። በአባቱም ቤት ሦስት ወር በእንክብካቤ አደገ። 21ወደ ውጭ በተጣለም ጊዜ የፈርዖን ልጅ አግኝታ ወሰደችው፤ እንደ ራሷ ልጅ አድርጋም አሳደገችው። 22ሙሴም የግብፆችን ጥበብ ሁሉ ተማረ፤ በንግግሩና በተግባሩም ብርቱ ሆነ።

23“ሙሴ አርባ ዓመት በሆነው ጊዜ፣ ወንድሞቹን የእስራኤልን ልጆች ሊጐበኝ በልቡ ዐሰበ። 24እርሱም፣ አንድ ግብፃዊ ከወገኖቹ አንዱን በደል ሲያደርስበት አይቶ ግብፃዊውንም ገደለ፤ ለተገፋው ወገኑም ተበቀለ። 25ወገኖቹም እግዚአብሔር በእርሱ እጅ ነጻ እንደሚያወጣቸው የሚያስተውሉ መስሎት ነበር፤ እነርሱ ግን አላስተዋሉም። 26በማግስቱም ደግሞ ሁለት እስራኤላውያን ሲጣሉ ደረሰ፤ ሊያስታርቃቸውም ፈልጎ፣ ‘ሰዎች፤ እናንተ እኮ ወንድማማቾች ናችሁ፤ እንዴት እርስ በርሳችሁ ትጐዳዳላችሁ?’ አላቸው።

27“በባልንጀራው ላይ በደል ሲያደርስ የነበረው ሰው ግን፣ ሙሴን ገፈተረውና እንዲህ አለ፤ ‘አንተን ገዥና ፈራጅ አድርጎ በእኛ ላይ የሾመህ ማን ነው? 28ወይስ ትናንት ግብፃዊውን እንደ ገደልኸው እኔንም ልትገድለኝ ትፈልጋልህን?’ 29ሙሴም ይህን እንደ ሰማ ሸሽቶ በምድያም አገር መጻተኛ ሆኖ ተቀመጠ፤ በዚያም ሁለት ወንዶች ልጆች ወለደ።

30“ከአርባ ዓመት በኋላ፣ በሲና ተራራ አካባቢ ባለው ምድረ በዳ፣ በሚነድድ ቍጥቋጦ ነበልባል ውስጥ መልአክ ተገለጠለት። 31ሙሴም ባየው ነገር ተደነቀ፤ ነገሩን ለማጣራት ወደዚያ ሲቀርብ የጌታ ድምፅ፤ 32‘እኔ የአባቶችህ አምላክ፣ የአብርሃም፣ የይስሐቅ፣ የያዕቆብ አምላክ ነኝ’ ሲል ሰማ። ሙሴም በፍርሀት ተዋጠ፤ ለመመልከትም አልደፈረም።

33“ጌታም እንዲህ አለው፤ ‘የእግርህን ጫማ አውልቅ፤ የቆምህባት ስፍራ የተቀደሰች ምድር ናትና። 34በግብፅ ያለውን የሕዝቤን መከራ በርግጥ አይቻለሁ፤ የጭንቅ ጩኸታቸውን ሰምቻለሁ፤ ላድናቸውም ወርጃለሁ። አሁንም ና፤ ወደ ግብፅ መልሼ እልክሃለሁ።’

35“እንግዲህ እነዚያ፣ ‘ገዥና ፈራጅ አድርጎ የሾመህ ማን ነው?’ ብለው የናቁትን ይህን ሙሴ እግዚአብሔር በቍጥቋጦው ውስጥ በታየው መልአክ አማካይነት ገዥና ታዳጊ አድርጎ ወደ እነርሱ ላከው። 36እርሱም መርቶ ከግብፅ አወጣቸው፤ በግብፅ፣ በቀይ ባሕርና በምድረ በዳ አርባ ዓመት ድንቅ ነገሮችንና ታምራዊ ምልክቶችን አደረገ።

37“የእስራኤልንም ሕዝብ፣ ‘እግዚአብሔር እንደ እኔ ያለ ነቢይ ከመካከላችሁ ያስነሣላችኋል’ ያላቸው ይኸው ሙሴ ነበር። 38እርሱም በሲና ተራራ ከተናገረው መልአክና ከአባቶቻችን ጋር በምድረ በዳ በሕዝቡ ጉባኤ መካከል ነበር፤ የሕይወትንም ቃል ወደ እኛ ለማስተላለፍ ተቀበለ።

39“አባቶቻችን ግን ተቃወሙት እንጂ ሊታዘዙት ስላልፈለጉ በልባቸው ወደ ግብፅ ተመለሱ። 40አሮንንም፣ ‘ፊት ፊታችን የሚሄዱ አማልክት አብጅልን፤ ከግብፅ ምድር መርቶ ያወጣን ያ ሙሴ ምን እንደ ደረሰበት አናውቅምና’ አሉት። 41በዚያን ጊዜ የጥጃ ምስል ሠርተው፣ ለጣዖቱ መሥዋዕት አቀረቡ፤ በእጃቸውም ሥራ ተደሰቱ፤ ፈነጠዙም። 42እግዚአብሔር ግን ከእነርሱ ዘወር አለ፤ ያመልኳቸውም ዘንድ ለሰማይ ከዋክብት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ይህም በነቢያት መጽሐፍ እንዲህ ተብሎ በተጻፈው መሠረት ተፈጸመ፤

“ ‘እናንት የእስራኤል ቤት ሆይ፤ አርባ ዓመት በምድረ በዳ በነበራችሁ ጊዜ፣

መሥዋዕትንና መባን ለእኔ አቀረባችሁልኝን?

43ይልቁንም ልታመልኳቸው የሠራችኋቸውን፣

የሞሎክን ድንኳንና የጣዖታችሁን፣

የሬምፉምን ኮከብ ከፍ ከፍ አድርጋችሁ ያዛችሁ።

ስለዚህ እኔም እንድትጋዙ አደርጋለሁ፤ ከባቢሎንም ወዲያ እሰድዳችኋለሁ።’

44“እግዚአብሔር ለሙሴ ባሳየው ንድፍና ባዘዘው መሠረት የተሠራችው የምስክር ድንኳን፣ ከአባቶቻችን ጋር በምድረ በዳ ነበረች። 45አባቶቻችንም ድንኳኗን ከተቀበሉ በኋላ፣ እግዚአብሔር በኢያሱ መሪነት ያሳደዳቸውን የአሕዛብን አገር በወረሱ ጊዜ ይዘዋት ገቡ፤ እስከ ዳዊትም ዘመን ድረስ በምድሪቱ ተቀመጠች፤ 46ዳዊትም በእግዚአብሔር ፊት ሞገስ በማግኘቱ ለያዕቆብ7፥46 አንዳንድ የጥንት ቅጆች የያዕቆብ ቤት ይላሉ። አምላክ ማደሪያ ያዘጋጅ ዘንድ ለመነ፤ 47ነገር ግን የማደሪያውን ቤት የሠራለት ሰሎሞን ነበር።

48“ይሁን እንጂ፣ ልዑል የሰው እጅ በሠራው ቤት ውስጥ አይኖርም፤ ይህም ነቢዩ እንዲህ ባለው መሠረት ነው፤

49“ ‘ሰማይ ዙፋኔ ነው፤

ምድርም የእግሬ ማሳረፊያ ናት፤

ታዲያ ምን ዐይነት ቤት ትሠሩልኛላችሁ?

ይላል ጌታ፤

ወይንስ ማረፊያ የሚሆነኝ የትኛው ቦታ ነው?

50ይህን ሁሉ የሠራው እጄ አይደለምን?’

51“እናንት ልባችሁና ጆሯችሁ ያልተገረዘ፣ ዐንገተ ደንዳኖች ልክ እንደ አባቶቻችሁ መንፈስ ቅዱስን ሁልጊዜ ትቃወማላችሁ። 52ከነቢያት መካከል አባቶቻችሁ ያላሳደዱት ማን አለ? የጻድቁን መምጣት አስቀድመው የተናገሩትን እንኳ ገድለዋል፤ እናንተም አሁን አሳልፋችሁ ሰጣችሁት፤ ገደላችሁትም፤ 53በመላእክት አማካይነት የተሰጣችሁንም ሕግ ተቀበላችሁ እንጂ አልጠበቃችሁትም።”

የእስጢፋኖስ መወገር

54በሸንጎው ስብሰባ ላይ የነበሩትም ይህን በሰሙ ጊዜ እጅግ ተቈጡ፤ ጥርሳቸውንም አፏጩበት። 55እስጢፋኖስ ግን በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ወደ ሰማይ ትኵር ብሎ ሲመለከት፣ የእግዚአብሔርን ክብር እንዲሁም ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አየና፣ 56“እነሆ፤ ሰማያት ተከፍተው፣ የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ቆሞ አያለሁ” አለ።

57በዚህ ጊዜ በታላቅ ድምፅ እየጮኹ ጆሯቸውን ደፍነው እርሱ ወደ አለበት በአንድነት ሮጡ፤ 58ይዘውም ከከተማው ውጭ ጣሉት፤ በድንጋይም ይወግሩት ጀመር። ይህ በሚሆንበት ጊዜ በዚያ የነበሩ ምስክሮችም ልብሳቸውን ሳውል በተባለ ጕልማሳ እግር አጠገብ አስቀመጡ።

59እስጢፋኖስም እየወገሩት ሳለ፣ “ጌታ ኢየሱስ ሆይ፤ ነፍሴን ተቀበላት፤” ብሎ ጸለየ፤ 60ከዚያም ተንበርክኮ በታላቅ ድምፅ፣ “ጌታ ሆይ፤ ይህን ኀጢአት አትቍጠርባቸው!” ብሎ ጮኸ፤ ይህን ካለ በኋላም አንቀላፋ።

Knijga O Kristu

Djela Apostolska 7:1-60

Stjepanov govor pred Vijećem

1Veliki svećenik ga upita: “Je li to istina?”

2Stjepan odgovori: “Braćo i časni oci, poslušajte me! Naš se slavni Bog ukazao našemu ocu Abrahamu u Mezopotamiji, prije nego što se nastanio u Haranu. 3Rekao mu je: ‘Idi iz svoje zemlje, iz svojega zavičaja, u zemlju koju ću ti pokazati.’7:3 Postanak 12:1. 4Abraham tako napusti kaldejsku zemlju i nastani se u Haranu. Odande ga je Bog, nakon smrti njegova oca, preselio u ovu zemlju u kojoj vi sada živite. 5Ali nije mu u njoj dao nikakvu baštinu, ni stopu zemlje, nego ju je obećao dati njemu i njegovim potomcima iako Abraham još nije imao djece. 6Bog mu je također rekao da će njegovi potomci živjeti u tuđoj zemlji kao robovi i da će ih ondje tlačiti četiri stotine godina. 7Ali rekao je: ‘Narodu kojemu će robovati ja ću suditi. A zatim će izići i klanjati mi se na ovomu mjestu.’7:5-7 Postanak 15:13-14. 8Zatim je Bog s Abrahamom sklopio savez obrezanja. Tako je Izak, Abrahamov sin, obrezan kad mu je bilo osam dana. Izak je tako učinio sa svojim sinom Jakovom, a Jakov s dvanaestoricom sinova, patrijarsima židovskoga naroda.

9A Jakovljevi sinovi, patrijarsi, bili su ljubomorni na svojega brata, Josipa, pa su ga prodali kao roba u Egipat. Ali Bog je bio s njim 10i izbavljao ga iz svih nevolja. Darivao ga je svojom naklonošću i mudrošću pred egipatskim kraljem, faraonom, te ga je on postavio za upravitelja Egipta i cijeloga svojeg dvora.

11Poslije je zavladala glad u cijelome Egiptu i Kanaanu. Naši su preci bili u velikoj nevolji: nisu mogli naći hrane. 12Jakov je čuo da u Egiptu ima žita pa je onamo poslao svoje sinove, naše pretke. 13Kad su drugi put otišli onamo, Josip je otkrio braći tko je, pa je faraon upoznao njegovu obitelj. 14Zatim je Josip poslao po svojega oca Jakova i svu svoju rodbinu da dođu u Egipat. Bilo ih je sedamdeset pet. 15Tako je Jakov došao u Egipat. Ondje su umrli on i njegovi sinovi, naši preci. 16Prenijeli su ih u Sihem i položili u grob koji je Abraham za srebro kupio od Hamorovih sinova.

17Kako se bližilo vrijeme ispunjenja obećanja koje je Bog dao Abrahamu, u Egiptu je naš narod rastao i množio se. 18Ali na egipatsko prijestolje dođe novi kralj, koji nije poznavao Josipa. 19Zlostavljao je naše pretke i primoravao roditelje da ostavljaju svoju novorođenčad da pomre.

20U to se doba rodio Mojsije. Bio je prelijepo dijete. Roditelji su se o njemu brinuli tri mjeseca. 21Kad su ga na koncu morali ostaviti, pronašla ga je faraonova kći i odgojila kao vlastitoga sina. 22Mojsije je poučen svoj egipatskoj mudrosti. Postao je silnim i u riječima i na djelima.

23Kad mu je bilo četrdeset godina, srce ga ponuka da posjeti svoje rođake, izraelski narod. 24Ondje ugleda kako neki Egipćanin zlostavlja Izraelca. Braneći zlostavljanog Izraelca, suprotstavi se Egipćaninu te se osveti i ubije ga. 25Mislio je da će njegova braća shvatiti kako ga je Bog poslao da ih spasi, ali oni nisu razumjeli.

26Sutradan opet ode k njima i ugleda kako se tuku dva Izraelca. Počne ih nagovarati da se pomire: ‘Ljudi!’ reče im. ‘Braća ste! Zašto zlostavljate jedni druge?!’

27Ali onaj koji je zlostavljao bližnjega odgurne Mojsija i reče: ‘Tko je tebe postavio poglavarom i sucem nad nama? 28Kaniš li i mene ubiti kao onoga Egipćanina jučer?’ 29Kad je to čuo, Mojsije pobjegne i skloni se u midjansku zemlju. Ondje su mu se rodila dva sina.

30Četrdeset godina nakon toga ukazao mu se anđeo u pustinji blizu gore Sinaja, u plamtećoj vatri gorućega grma. 31Mojsije je opazio gorući grm i zadivljen se pitao što je to. Dok je prilazio da bolje pogleda, začuje Gospodnji glas: 32‘Ja sam Abrahamov, Izakov i Jakovljev Bog.’ Mojsije se silno preplaši. Nije se usuđivao gledati.

33Gospodin mu reče: ‘Izuj sandale s nogu jer stojiš na svetoj zemlji. 34Dobro sam vidio nevolju svojega naroda u Egiptu i čuo njegove uzdahe. Sišao sam da ga izbavim. Idi sada! Šaljem te u Egipat!’7:31-34 Izlazak 3:5-10.

35Toga istog Mojsija kojega su se odrekli pitajući ga: ‘Tko je tebe postavio poglavarom i sucem nad nama?’ Bog im je poslao kao poglavara i otkupitelja da ih izbavi, preko anđela koji mu se ukazao u gorućem grmu. 36On ih je izveo iz Egipta čineći čudesa i znakovlje. Vodio ih je kroz Crveno more i kroz pustinju četrdeset godina.

37Taj je isti Mojsije rekao izraelskome narodu: ‘Bog će vam podignuti proroka poput mene iz vašega vlastitog naroda.’7:37 Ponovljeni zakon 18:15. 38Isti je Mojsije bio posrednikom između izraelskoga naroda i anđela koji mu je dao riječi života na gori Sinaju da ih preda nama.

39Naši preci nisu mu se htjeli pokoriti, nego su ga odbili i srcima se opet okrenuli prema Egiptu. 40Rekli su Aronu: ‘Napravi nam bogove koji će ići pred nama jer ne znamo što se dogodilo s Mojsijem koji nas je izveo iz Egipta!’ 41Načinili su idola u obliku teleta, prinijeli mu žrtve i veselili se tomu što su učinili. 42A Bog se okrenuo od njih i pustio ih da se klanjaju suncu, mjesecu i zvijezdama kao svojim bogovima. U proročkoj je knjizi zapisano:

‘Zar ste meni prinosili žrtve

za četrdeset godina u pustinji, Izraele?

43Ne; okrenuli ste se poganskim bogovima—

Molohovu svetištu

i zvijezdi boga Refana,

likovima koje ste načinili da biste im se klanjali.

Zato ću vas odvesti u progonstvo

dalje od Babilona!’7:42-43 Amos 5:25-27.

44Naši su preci sa sobom kroz pustinju nosili Šator svjedočanstva. Bio je načinjen točno prema predlošku koji je Mojsiju pokazao Bog. 45Mnogo godina zatim, kad je Jošua ratovao protiv poganskih naroda koje je Bog istjerao iz te zemlje, Šator su unijeli sa sobom u novu zemlju. Ondje je ostao sve do vremena kralja Davida.

46Davidu je Bog bio milostiv, te ga je zamolio za dopuštenje da izgradi Hram Jakovljevu Bogu. 47Ali izgradio ga je tek Salomon. 48Ipak, Svevišnji ne prebiva u hramovima koje su izgradile ljudske ruke. Kao što kaže prorok:

49‘Nebo mi je prijestolje,

a zemlja podnožje mojim nogama.

Kakav mi vi dom možete izgraditi?

Gdje da počivam?

50Zar nije moja ruka stvorila sve u nebu i na zemlji?’7:49-50 Izaija 66:1-2.

51Tvrdoglavi ste! Pogani ste u srcima i gluhi za istinu!7:51 U grčkome: neobrezanih srca i ušiju. Uvijek se opirete Svetome Duhu, baš kao i vaši preci! 52Ima li ijedan prorok kojega vaši oci nisu progonili? Pobili su one koji su pretkazali dolazak Pravednika—kojega ste vi izdali i smaknuli. 53Preko anđela ste dobili Zakon, a niste ga se držali!”

54Kad su to čuli, židovski se vođe toliko razgnjeve na Stjepana da na njega počnu škripati zubima. 55Ali Stjepan, pun Svetoga Duha, upre pogled u nebo i ugleda Božju slavu i Isusa kako stoji na počasnome mjestu, Bogu zdesna. 56“Vidim otvorena nebesa”, reče, “i Sina Čovječjega kako stoji zdesna Bogu.”

57Oni nato rukama poklope uši i vičući iz svega glasa složno navale na njega. 58Izvuku ga iz grada i počnu kamenovati. Svjedoci odlože ogrtače do nogu mladića Savla.7:58 Savao se također zove Pavao. Vidjeti: 13:9.

59Dok su ga kamenovali, Stjepan je zazivao: “Gospodine Isuse, primi moj duh!” 60Zatim se baci na koljena i poviče iz sve snage: “Gospodine, ne uzmi im ovo za grijeh!” Pošto to izgovori, izdahne.