ሐዋርያት ሥራ 6 – NASV & CRO

New Amharic Standard Version

ሐዋርያት ሥራ 6:1-15

የሰባቱ ዲያቆናት መመረጥ

1የደቀ መዛሙርት ቍጥር እየጨመረ በሄደበት በዚህ ወቅት፣ ከግሪክ አገር የመጡ አይሁድ በይሁዳ ይኖሩ በነበሩት አይሁድ ላይ አጕረመረሙ፤ ምክንያቱም በየዕለቱ በሚከናወነው ምግብ የማደል አሠራር ላይ ከእነርሱ ወገን የሆኑት መበለቶች ችላ ተብለው ነበር። 2ስለዚህ ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ሌሎችን ደቀ መዛሙርት በአንድነት ሰብስበው እንዲህ አሉ፤ “እኛ የማእዱን አገልግሎት ለማስተናገድ ስንል የእግዚአብሔርን ቃል አገልግሎት መተው አይገባንም። 3ስለዚህ ወንድሞች ሆይ፤ ከእናንተ መካከል በመንፈስ ቅዱስና በጥበብ የተሞሉ ለመሆናቸው የተመሰከረላቸውን ሰባት ሰዎች ምረጡ፤ ይህን ኀላፊነት ለእነርሱ እንሰጣለን፤ 4እኛ ግን በጸሎትና በቃሉ አገልግሎት እንተጋለን።”

5አባባሉ ሁላቸውን ደስ አሰኘ፤ በእምነትና በመንፈስ ቅዱስ የተሞላውን እስጢፋኖስን እንዲሁም ፊልጶስን፣ ጵሮኮሮስን፣ ኒቃሮናን፣ ጢሞናን፣ ጰርሜናንና ወደ ይሁዲነት ገብቶ የነበረውን አንጾኪያዊውን ኒቆላዎስን መረጡ። 6እነዚህንም አምጥተው ሐዋርያት ፊት አቀረቧቸው፤ እነርሱም ከጸለዩ በኋላ እጃቸውን ጫኑባቸው።

7የእግዚአብሔርም ቃል እየሰፋ ሄደ፤ የደቀ መዛሙርቱም ቍጥር በኢየሩሳሌም እጅግ እየበዛ ሄደ፤ ከካህናትም ብዙዎቹ ለእምነት የታዘዙ ሆኑ።

የእስጢፋኖስ መያዝ

8በዚህ ጊዜ እስጢፋኖስ ጸጋንና ኀይልን ተሞልቶ በሕዝቡ መካከል ድንቅ ነገሮችንና ታምራዊ ምልክቶችን ያደርግ ነበር። 9“የነጻ ወጪዎች ምኵራብ” ተብሎ የሚጠራው ምኵራብ አባላት የሆኑ ከቀሬናና ከእስክንድርያ፣ እንዲሁም ከኪልቅያና ከእስያ አውራጃዎች የመጡ ሰዎችም ተቃውሞ አስነሥተው እስጢፋኖስን ይከራከሩት ጀመር፤ 10ይሁን እንጂ ይናገርበት የነበረውን ጥበብና መንፈስ መቋቋም አልቻሉም።

11ስለዚህ፣ “እስጢፋኖስ በሙሴና በእግዚአብሔር ላይ የስድብ ቃል ሲሰነዝር ሰምተናል” የሚሉ ሰዎችን በስውር አዘጋጁ።

12በዚህ ሁኔታ ሕዝቡን፣ የአገር ሽማግሌዎቹንና የሕግ መምህራኑን በማነሣሣት፣ እስጢፋኖስን አስይዘው በአይሁድ ሸንጎ ፊት አቀረቡት፤ 13እንዲህ ብለው የሚመሰክሩ የሐሰት ምስክሮችንም አቆሙበት፤ “ይህ ሰው በዚህ በተቀደሰው ስፍራና በሕጉ ላይ የስድብ ቃል መናገሩን በፍጹም አልተወም፤ 14ምክንያቱም ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ ይህን ስፍራ እንደሚያጠፋና ከሙሴ የተቀበልነውን ወግ እንደሚለውጥ ሲናገር ሰምተነዋል።”

15በሸንጎው ተቀምጠው የነበሩትም ሁሉ እስጢፋኖስን ትኵር ብለው ሲመለከቱት ፊቱ የመልአክ ፊት መስሎ ታያቸው።

Knijga O Kristu

Djela Apostolska 6:1-15

Apostoli biraju sedmoricu

1Ali kako je broj vjernika6:1 U grčkome: učenika. Isto i u 6:2, 7. naglo rastao, neki se počnu žaliti. Židovi koji su govorili grčki prigovarali su Židovima koji su govorili hebrejski da zanemaruju njihove udovice u svagdanjem dijeljenju pomoći. 2Dvanaestorica zato sazovu vjernike.

“Mi apostoli ne bismo trebali služiti pri stolovima umjesto da propovijedamo i poučavamo Riječ. 3Pronađite, braćo, među sobom sedam ljudi na dobrome glasu, punih Svetoga Duha i mudrosti. Njih ćemo za to zadužiti, 4a mi ćemo se posvetiti molitvi te propovijedanju i poučavanju Riječi.”

5Prijedlog se svima svidio. Izaberu Stjepana, čovjeka punog vjere i Svetoga Duha, te Filipa, Prohora, Nikanora, Timona, Parmenu i Nikolu koji je došao iz Antiohije. On se kao poganin obratio na židovsku vjeru, a sada je postao kršćaninom. 6Postave njih sedmoricu pred apostole, a oni polože na njih ruke i pomole se.

7Božja riječ sve se više širila. Broj vjernika u Jeruzalemu naglo je rastao, a i mnogi su židovski svećenici prihvaćali vjeru.

Stjepanovo uhićenje

8Stjepan je bio pun Božje milosti i sile. Činio je među narodom silna čudesa i znamenje. 9Ali pobune se neki iz takozvane sinagoge Slobodnjaka, Židovi iz Cirene, Aleksandrije, Cilicije i Male Azije, pa počnu s njime raspravljati. 10Nitko od njih nije se mogao nositi s mudrošću i Duhom kojim je Stjepan govorio.

11Nagovore zato neke ljude da za njega kažu: “Čuli smo ga da govori pogrdne riječi protiv Mojsija i protiv Boga.” 12Podjarili su i narod i starješine i pismoznance. Oni dođu po njega, ščepaju ga i odvuku u Vijeće. 13Dovedu onamo krivokletnike koji izjave: “Ovaj čovjek uvijek govori protiv Hrama i protiv Mojsijeva zakona. 14Čuli smo da kaže kako će taj Isus iz Nazareta uništiti Hram i promijeniti običaje koje nam je Mojsije predao.” 15Svi koji su sjedili u Vijeću pogledaju u Stjepana i opaze da mu je lice poput anđeoskog.