ሆሴዕ 3 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 3:1-5

የሆሴዕ ከሚስቱ ጋር መታረቅ

1እግዚአብሔር እንዲህ አለኝ፤ “እርሷ በሌላ ሰው የምትወደድ አመንዝራ ብትሆንም፣ አሁንም ሂድና ሚስትህን ውደዳት፤ ወደ ሌሎች አማልክት ዘወር ቢሉና ለእነርሱም የተቀደሰውን የዘቢብ ጥፍጥፍ ቢወድዱም፣ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን እንደ ወደዳቸው አንተም እርሷን ውደዳት።”

2ስለዚህ በዐሥራ አምስት ሰቅል ጥሬ ብርና በአንድ ቆሮስ ተኩል መስፈሪያ ገብስ ገዛኋት። 3እኔም፣ “ከእኔ ጋር ብዙ ቀን ተቀመጪ፤3፥3 ወይም ቈዪ አታመንዝሪ ወይም ሌላ ሰው አትውደጂ፤ እኔም ከአንቺ ጋር እኖራለሁ” ብዬ ነገርኋት።

4እስራኤላውያን ለብዙ ዘመን ያለ ንጉሥና ያለ አለቃ፣ ያለ መሥዋዕትና ያለ ዐምደ ጣዖት፣ ያለ ኤፉድና ያለ ጣዖት ምስል ይኖራሉና። 5ከዚያ በኋላ እስራኤላውያን ተመልሰው አምላካቸውን እግዚአብሔርንና ንጉሣቸውን ዳዊትን ይፈልጋሉ፤ በመጨረሻውም ዘመን በመንቀጥቀጥ ወደ እግዚአብሔርና ወደ በረከቱ ይመጣሉ።

Thai New Contemporary Bible

โฮเชยา 3:1-5

โฮเชยาคืนดีกับภรรยา

1องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสกับข้าพเจ้าว่า “จงไปแสดงความรักแก่ภรรยาของเจ้าอีกครั้ง แม้ว่ามีคนอื่นรักนางอยู่และนางคบชู้ จงรักนางเหมือนที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงรักชนอิสราเอล แม้ว่าพวกเขาหันไปหาพระอื่นๆ และรักขนมลูกเกดที่ถวายแก่พระเหล่านั้น”

2ดังนั้นข้าพเจ้าจึงซื้อตัวนางคืนมาด้วยเงินหนัก 15 เชเขล3:2 1 เชเขล คือเงินหนักประมาณ 11.5 กรัม มีค่าเท่ากับค่าแรงสองเดือน และข้าวบาร์เลย์ประมาณ 330 ลิตร3:2 ภาษาฮีบรูว่า1 โฮเมอร์กับ 1 เลเธค 3ข้าพเจ้าจึงบอกนางว่า “เจ้าจะต้องอยู่กับเราหลายวัน เจ้าต้องเลิกทำตัวเป็นโสเภณี และไม่ทำตัวใกล้ชิดกับชายใดๆ แล้วเราจะอยู่กับ3:3 หรือรอคอยเจ้า”

4ฉะนั้นชาวอิสราเอลจึงอยู่โดยไม่มีกษัตริย์หรือเจ้านาย ไม่มีการถวายเครื่องบูชาหรือมีศิลาศักดิ์สิทธิ์ ไม่มีเอโฟดหรือรูปเคารพเป็นเวลานาน 5หลังจากนั้นชนชาติอิสราเอลจะกลับมาแสวงหาพระยาห์เวห์พระเจ้าของเขาและดาวิดกษัตริย์ของเขา พวกเขาจะตัวสั่นเข้ามาหาองค์พระผู้เป็นเจ้าและกลับมาหาพระพรของพระองค์ในบั้นปลาย