ሆሴዕ 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ሆሴዕ 4:1-19

በእስራኤል ላይ የቀረበ ክስ

1በምድሪቱ በምትኖሩ በእናንተ ላይ

እግዚአብሔር የሚያቀርበው ክስ ስላለው፣

እናንት እስራኤላውያን ይህን የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤

“ታማኝነት የለም፤ ፍቅርም የለም፤

እግዚአብሔርንም ማወቅ በምድሪቱ የለም።

2በዚያ ያለው ርግማን4፥2 መርገምን ያመለክታል፣ መዋሸት፣ መግደል፣

መስረቅና ማመንዘር ብቻ ነው፤

ቃል ኪዳንን ሁሉ ያፈርሳሉ፤

ደም ማፍሰስና ግድያ ይበዛል።

3ስለዚህ ምድሪቱ አለቀሰች፤4፥3 ወይም ደረቀች

በውስጧም የሚኖሩ ሁሉ ኰሰመኑ፤

የምድር አራዊት፣ የሰማይ ወፎች፣

የባሕርም ዓሦች ዐለቁ።

4“ነገር ግን ማንም ሰው አይከራከር፤

ማንም ሌላውን አይወንጅል፤

በካህናት ላይ ክስን እንደሚያቀርቡ፣

ሕዝብህ እንደዚያው ናቸውና።

5ቀንና ሌሊት ትደናበራላችሁ፤

ነቢያትም ከእናንተ ጋር ይደናበራሉ፤

ስለዚህ እናታችሁን አጠፋታለሁ፤

6ሕዝቤ ዕውቀት ከማጣቱ የተነሣ ጠፍቷል።

“ዕውቀትን ስለ ናቃችሁ፣

እኔም ካህናት እንዳትሆኑ ናቅኋችሁ፤

የአምላካችሁን ሕግ ስለ ረሳችሁ፣

እኔም ልጆቻችሁን እረሳለሁ።

7ካህናት በበዙ ቍጥር፣

በእኔ ላይ የሚያደርጉት ኀጢአት በዝቷል፤

ክብራቸውንም4፥7 ማሶሬቲክ የሚለው እንዲሁ ሲሆን የጥንት ዕብራውያን ጸሐፍት ትውፊት ግን ክብሬን ይላል። በውርደት ለውጠዋል።4፥7 ሱርስትና የጥንት ዕብራውያን ጸሐፍት ትውፊት የሚሉት እንዲሁ ሲሆን፣ ማሶሬቲክ ግን እለውጠዋለሁ ይላል።

8የሕዝቤ ኀጢአት ለመብል ሆኖላቸዋል፤

ርኩሰታቸውንም እጅግ ወደዱ።

9ካህናትም ከሕዝቡ የተለዩ አይደሉም፤

ሁሉንም እንደ መንገዳቸው እቀጣቸዋለሁ፤

እንደ ሥራቸውም እከፍላቸዋለሁ።

10“ይበላሉ ግን አይጠግቡም፤

ያመነዝራሉ ግን አይበዙም፤

እግዚአብሔርን በመተው፣

ራሳቸውን 11ለአመንዝራነት፣

ለአሮጌና ለአዲስ የወይን ጠጅ አሳልፈው ሰጡ፤

በእነዚህም የሕዝቤ ማስተዋል ተወሰደ፤

12ከዕንጨት የተሠራውን ጣዖት ምክር ይጠይቃሉ፤

ዘንጋቸውም ይመልስላቸዋል።

የአመንዝራነት መንፈስ ያስታቸዋል፤

ለአምላካቸውም ታማኝ አልሆኑም።

13በተራሮችም ጫፍ ላይ ይሠዋሉ፤

መልካም ጥላ ባለው፣ በባሉጥ፣

በኮምቦልና በአሆማ ዛፍ ሥር፣

በኰረብቶችም ላይ የሚቃጠል ቍርባን ያቀርባሉ።

ስለዚህ ሴቶች ልጆቻችሁ ዘማውያን፣

ምራቶቻችሁም አመንዝራዎች ይሆናሉ።

14“ሴቶች ልጆቻችሁ ዘማውያን ሲሆኑ፣

የልጆቻችሁም ሚስቶች ሲያመነዝሩ

አልቀጣቸውም።

ወንዶች ከጋለሞቶች ጋር ይሴስናሉ፤

ከቤተ ጣዖት ዘማውያን ጋር ይሠዋሉና፤

የማያስተውል ሕዝብ ወደ ጥፋት ይሄዳል!

15“እስራኤል ሆይ፤ አንቺ ብታመነዝሪም፣

ይሁዳ በበደለኛነት አትጠየቅ።

“ወደ ጌልገላ አትሂዱ፤

ወደ ቤትአዌንም4፥15 ቤትአዌን የእግዚአብሔር ቤት የተባለችው ቤቴል ስትሆን፣ የቃሉ ትርጕም የክፋት ቤት ማለት ነው። አትውጡ፤

‘ሕያው እግዚአብሔርን’ ብላችሁም አትማሉ።

16እስራኤላውያን እንደ እልኸኛ ጊደር፣

እልኸኞች ናቸው፤

ታዲያ እግዚአብሔር እነርሱን በመልካም መስክ ውስጥ እንዳሉ የበግ ጠቦቶች

እንዴት ያሰማራቸዋል?

17ኤፍሬም ከጣዖት ጋር ተጣምሯል፤

እስቲ ተዉት፤

18መጠጣቸው ባለቀ ጊዜ እንኳ፣

ዘማዊነታቸውን አያቆሙም፤

ገዦቻቸውም ነውርን አጥብቀው ይወድዳሉ።

19ዐውሎ ነፋስ ጠራርጎ ይወስዳቸዋል፤

መሥዋዕቶቻቸውም ኀፍረት ያመጡባቸዋል።”

Thai New Contemporary Bible

โฮเชยา 4:1-19

ข้อกล่าวหาต่ออิสราเอล

1ชนอิสราเอลทั้งหลาย จงฟังพระดำรัสขององค์พระผู้เป็นเจ้า

เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงมีข้อกล่าวหา

ต่อเจ้าผู้อาศัยอยู่ในดินแดนนี้ ความว่า

“ในดินแดนนี้ไม่มีความซื่อสัตย์ ไม่มีความรัก

ไม่ยอมรับรู้พระเจ้า

2มีแต่การสาปแช่ง4:2 คือ การกล่าวคำสาปแช่ง การโกหก และการเข่นฆ่า

การลักขโมย และการล่วงประเวณี

พวกเขาละเมิดพันธะผูกพันต่างๆ

และเข่นฆ่ากันครั้งแล้วครั้งเล่า

3ด้วยเหตุนี้แผ่นดินจึงโศกเศร้าคร่ำครวญ4:3 หรือแห้งแล้ง

และทุกคนที่อาศัยอยู่ในดินแดนนี้ก็เสื่อมสูญไป

สัตว์ในท้องทุ่ง นกในอากาศ

และปลาในทะเลกำลังจะตายไป

4“แต่อย่าให้ใครฟ้องร้อง

อย่าให้ใครกล่าวโทษคนอื่น

เพราะประชากรของเจ้า

ก็เป็นเหมือนคนที่ฟ้องร้องกล่าวโทษปุโรหิต

5เจ้าสะดุดล้มทั้งวันทั้งคืน

และบรรดาผู้พยากรณ์ก็สะดุดล้มไปกับเจ้า

ฉะนั้นเราจะทำลายมารดาของเจ้า

6ประชากรของเราถูกทำลายไปเพราะขาดความรู้

“เนื่องจากเจ้าปฏิเสธความรู้

เราจึงไม่ยอมรับว่าพวกเจ้าเป็นปุโรหิตของเรา

เนื่องจากเจ้าเพิกเฉยต่อบทบัญญัติของพระเจ้าของเจ้า

เราจึงเพิกเฉยต่อลูกๆ ของเจ้า

7จำนวนปุโรหิตเพิ่มมากขึ้นเท่าใด

พวกเขาก็ยิ่งทำบาปต่อเรามากขึ้นเท่านั้น

พวกเขาได้แลก4:7 ฉบับ MT. ว่าเราจะแลกองค์ผู้ทรงเกียรติสิริของพวกเขา4:7 สำเนาต้นฉบับภาษาฮีบรูโบราณว่าของเรากับสิ่งที่น่าละอาย

8พวกเขาเลี้ยงชีพด้วยบาปของประชากรของเรา

และชื่นชอบความชั่วร้ายของพวกเขา

9และจะเป็นเช่นนี้คือ ประชาชนเป็นอย่างไรปุโรหิตก็เป็นอย่างนั้น

เราจะลงโทษทั้งสองฝ่ายเนื่องด้วยวิถีความประพฤติของพวกเขา

และตอบสนองการกระทำของพวกเขา

10“พวกเขาจะกิน แต่ไม่อิ่ม

พวกเขาจะเข้าไปเกี่ยวข้องกับการเป็นโสเภณี แต่จะไม่มีลูก

เพราะพวกเขาละทิ้งองค์พระผู้เป็นเจ้า

ยอมตัว 11เป็นโสเภณี

ปล่อยตัวไปกับเหล้าองุ่นทั้งเก่าและใหม่

ซึ่งสิ่งเหล่านี้ได้ริบความเข้าใจไปจากพวกเขา

12ประชากรของเราไปปรึกษารูปเคารพไม้

อาศัยคำตอบจากไม้เสี่ยงโชค

วิญญาณแห่งการเป็นโสเภณีชักนำเขาให้หลงเตลิด

เขาไม่ซื่อสัตย์ต่อพระเจ้าของเขา

13เขาถวายเครื่องบูชาบนยอดเขา

และเผาเครื่องบูชาต่างๆ บนเนินเขา

ใต้ต้นโอ๊ก ต้นปอปลาร์ และต้นเทเลบินธ์

ซึ่งแผ่ร่มเงาเย็นสบาย

ฉะนั้นลูกสาวทั้งหลายของเจ้าก็หันไปเป็นโสเภณี

และลูกสะใภ้ของเจ้าก็คบชู้

14“เราจะไม่ลงโทษลูกสาวของเจ้า

เมื่อพวกเขาหันไปเป็นโสเภณี

หรือลงโทษลูกสะใภ้ของเจ้า

ที่ไปคบชู้

เพราะพวกผู้ชายเองก็ไปคบค้ากับโสเภณี

และทอดตัวให้กับหญิงโสเภณีประจำเทวสถานต่างๆ

ประชาชาติที่ไม่มีความเข้าใจจะถึงแก่ความพินาศ!

15“อิสราเอลเอ๋ย แม้เจ้าจะคบชู้

ก็อย่าให้ยูดาห์ทำผิดไป

“อย่าไปที่กิลกาล

อย่าไปยังเบธอาเวน4:15 แปลว่าบ้านแห่งความชั่วร้าย(แทนที่จะเรียกว่าเบธเอลซึ่งแปลว่าพระนิเวศของพระเจ้า)

และอย่าสาบานโดยกล่าวว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงพระชนม์อยู่แน่ฉันใด!’

16ชนอิสราเอลดื้อ

เหมือนวัวสาวที่ดื้อรั้น

แล้วองค์พระผู้เป็นเจ้าจะทรงเลี้ยงดูเขา

เหมือนลูกแกะในทุ่งหญ้าได้อย่างไร?

17เอฟราอิมไปยึดติดกับรูปเคารพ

จงปล่อยเขาไว้ตามลำพังเถิด!

18แม้เครื่องดื่มของพวกเขาจะหมดไปแล้ว

พวกเขาก็ยังคงทำตัวเป็นโสเภณีต่อไป

บรรดาผู้ปกครองของเขารักใคร่หลงใหลวิถีอันน่าอับอาย

19ลมพายุหมุนจะกวาดซัดพวกเขาไป

และเครื่องบูชาต่างๆ ของพวกเขาจะนำความอัปยศอดสูมาถึงพวกเขา