約書亞記 23 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約書亞記 23:1-16

約書亞的訣別之言

1此後很長時間,耶和華使以色列人四境太平,沒有戰事。約書亞年事已高, 2他召來了以色列的長老、族長、審判官和官長,對他們說:「我已經老了, 3你們都親眼看見你們的上帝耶和華怎樣為了你們而對付列邦,親自為你們爭戰。 4約旦河到地中海的這片土地,無論是已征服的還是沒有征服的,我已經用抽籤的方式分給你們各支派作產業。 5你們的上帝耶和華必把列邦從你們面前趕出去,使他們離開你們。這樣,你們就可以承受他們的土地,正如你們的上帝耶和華的應許。 6所以,你們應當剛強,謹遵摩西律法書上所記載的一切,不可有半點偏離。 7不可與你們中間剩下的異族混雜,不可提他們的神明或憑它們起誓,不可供奉、祭拜他們的神明。 8你們要一如既往地倚靠你們的上帝耶和華, 9因為祂為你們趕走了強大的外族人,至今無人敵得過你們。 10你們一個人能打敗他們一千人,因為你們的上帝耶和華照著祂的應許為你們爭戰。 11所以你們要特別謹慎,愛你們的上帝耶和華。 12如果你們悖逆,跟你們當中剩下的異族人聯合,通婚往來, 13毫無疑問,你們的上帝耶和華必不再為你們趕走他們。相反,他們還要成為設在你們當中的圈套和陷阱,你們的肉中刺、眼中釘,直到你們在你們的上帝耶和華所賜給你們的這塊美好的土地上滅亡。

14「我快要走完人世的路程了。你們深知你們的上帝耶和華賜給你們的一切美好應許沒有一句落空,都已經應驗了。 15正如你們的上帝耶和華已成就祂應許給你們的一切福氣,如果你們違背祂,祂必照樣降各樣災禍給你們,直到把你們從祂所賜的這美好土地上毀滅。 16你們如果違背你們的上帝耶和華吩咐你們遵守的約,去供奉、祭拜別的神明,祂必向你們發怒,使你們在祂所賜的這美好土地上迅速滅亡。」

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 23:1-16

ኢያሱ ለመሪዎች የተናገረው የመሰናበቻ ቃል

1እግዚአብሔር እስራኤላውያንን በዙሪያቸው ካሉት ጠላቶቻቸው ሁሉ ካሳረፋቸው እነሆ፣ ብዙ ዘመን ዐለፈ፤ በዚህ ጊዜ ኢያሱ በጣም አርጅቶ፣ ዕድሜውም ገፍቶ ነበር። 2ኢያሱ እስራኤልን ሁሉ አለቆቻቸውን፣ መሪዎቻቸውን፣ ፈራጆቻቸውንና ሹማምታቸውን በሙሉ ጠርቶ እንዲህ አላቸው፤ “እኔ አርጅቻለሁ፤ ዕድሜዬም ገፍቷል። 3አምላካችሁ እግዚአብሔር ስለ እናንተ ሲል በእነዚህ ሕዝቦች ሁሉ ላይ ያደረገውን ማናቸውንም ነገር እናንተው ራሳችሁ አይታችኋል፤ ስለ እናንተ የተዋጋላችሁ ራሱ አምላካችሁ እግዚአብሔር ነው። 4ከዮርዳኖስ አንሥቶ በስተ ምዕራብ እስካለው እስከ ታላቁ ባሕር23፥4 የሚድትራንያን ባሕር ነው። ድረስ በሙሉ ካሸነፍኋቸው ሕዝቦች ያልወረሳችሁትን ቀሪ ምድር ርስት እንዲሆን ለየነገዶቻችሁ እንዴት አድርጌ በዕጣ እንዳከፋፈልኋችሁ አስታውሱ። 5ራሱ አምላካችሁ እግዚአብሔር ከፊታችሁ ያስወግዳቸዋል፤ ከፊታችሁም ያሉበትን ስፍራ ያስለቅቃቸዋል፤ አምላካችሁ እግዚአብሔር በሰጣችሁም ተስፋ መሠረት ምድራቸውን ትወርሳላችሁ።

6“በርቱ፤ ወደ ግራም ወደ ቀኝም ሳትሉ በሙሴ የሕግ መጽሐፍ የተጻፈውን ሁሉ ለመጠበቅና ለማድረግ እጅግ በርቱ። 7በመካከላችሁ ከቀሩት ከእነዚህ ሕዝቦች ጋር አትተባበሩ፤ የአማልክታቸውን ስም አትጥሩ፤ አትማሉባቸው፤ አታገልግሏቸው፤ አትስገዱላቸውም፤ 8ነገር ግን እስካሁን እንዳደረጋችሁት ሁሉ አምላካችሁን እግዚአብሔርን አጥብቃችሁ ያዙ።

9እግዚአብሔር ታላላቅና ኀያላን ሕዝቦችን ከፊታችሁ አሳድዶ አስወጥቷቸዋል፤ እስከ ዛሬም ድረስ ማንም ሊቋቋማችሁ አልቻለም። 10አምላካችሁ እግዚአብሔር በሰጣችሁ ተስፋ መሠረት የሚዋጋላችሁ ስለሆነ፣ ከእናንተ አንዱ ሰው ሺውን ያሳድዳል። 11ስለዚህ አምላካችሁን እግዚአብሔርን ለመውደድ ተጠንቀቁ።

12“ነገር ግን ከእርሱ ተመልሳችሁ ተርፈው በመካከላችሁ ከሚገኙት ከእነዚህ ሕዝቦች ጋር ብትተባበሩ፣ በጋብቻም ብትተሳሰሩና ብትቀላቀሉ፣ 13አምላካችሁ እግዚአብሔር ከእንግዲህ ከፊታችሁ እንደማያወጣቸው ይህን ልታውቁ ይገባል፤ አምላካችሁ እግዚአብሔር ከሰጣችሁ ከዚህች መልካም ምድር እስክትጠፉ ድረስም ወጥመድና አሽክላ፣ ለጀርባችሁ ጅራፍ፣ ለዐይኖቻችሁም እሾኽ ይሆኑባችኋል።

14“እነሆ፤ አሁን የምድርን ሁሉ መንገድ ልሄድ ነው፤ አምላካችሁ እግዚአብሔር ከሰጣችሁ መልካም ተስፋ ሁሉ አንዲቱን እንኳ እንዳላስቀረባችሁ፣ በፍጹም ልባችሁ በፍጹም ነፍሳችሁ ታውቃላችሁ፤ አንዱም ሳይቀር ሁሉም ተፈጽሟል። 15ነገር ግን አምላካችሁ እግዚአብሔር የሰጣችሁ መልካሙ ተስፋ በሙሉ እንደ ተፈጸመ ሁሉ፣ እንደዚሁም አምላካችሁ እግዚአብሔር ከሰጣችሁ ከመልካሚቱ ምድር እስኪያጠፋችሁ ድረስ ክፉውን ነገር ያመጣባችኋል። 16አምላካችሁ እግዚአብሔር ያዘዛችሁን ኪዳን ብታፈርሱ፣ ሄዳችሁም ሌሎችን አማልክት ብታገለግሉና ብትሰግዱላቸው የእግዚአብሔር ቍጣ በላያችሁ ይነድዳል፤ ከሰጣችሁም ከመልካሚቱ ምድር በፍጥነት ትጠፋላችሁ።”