約書亞記 24 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

約書亞記 24:1-33

重申耶和華的約

1約書亞示劍招聚以色列各支派,然後召來以色列的長老、族長、審判官和官長。他們一同站在上帝面前。 2約書亞對全體民眾說:「以色列的上帝耶和華這樣說,『從前你們的祖先,包括亞伯拉罕拿鶴二人的父親他拉,住在幼發拉底河那邊拜別的神明。 3我把你們的祖先亞伯拉罕幼發拉底河那邊帶出來,領他走遍迦南,使他人丁興旺。我把以撒賜給他, 4雅各以掃賜給以撒,把西珥山賜給以掃作產業,雅各和他的子孫則去了埃及5後來,我差遣摩西亞倫埃及,並用瘟疫攻擊埃及人,把你們領出來。 6我引領你們的祖先離開埃及來到紅海的時候,埃及人帶領戰車騎兵追了上來。 7你們的祖先大聲呼求我,我就降下黑暗,把你們和埃及人分開,又用海水淹沒埃及人。你們親眼見過我在埃及的作為。後來,你們在曠野度過了一段漫長的歲月。 8我領你們來到約旦河東邊亞摩利人居住的地方。他們跟你們爭戰,我把他們交在你們手中,使你們佔領他們的土地作自己的產業。我把他們從你們面前全部消滅。 9那時,摩押西撥的兒子巴勒起兵攻打你們,並派人去召比珥的兒子巴蘭來咒詛你們。 10我不但沒有聽巴蘭的話,反而使他為你們連連祝福。這樣,我從巴勒手中救了你們。 11你們過了約旦河來到耶利哥耶利哥人、亞摩利人、比利洗人、迦南人、人、革迦撒人、希未人和耶布斯人都跟你們交戰,但我把他們交在你們手中。 12我差黃蜂飛在你們前面,把亞摩利的兩個王從你們面前趕走,沒有動用你們一刀一弓。 13你們沒有開墾土地,也沒有建造城邑,但我賜給你們土地和城邑,使你們住在其中,享用別人栽種的葡萄園和橄欖園的果子。』

14「所以,你們要敬畏耶和華,誠心誠意地事奉祂,摒棄你們祖先在幼發拉底河那邊和在埃及所拜的神明,專心事奉耶和華。 15如果你們不願意事奉耶和華,今天就選擇你們的神明吧,或大河那邊你們祖先事奉的神明,或你們這裡亞摩利人的神明。至於我和我全家,我們必事奉耶和華。」

16民眾答道:「我們決不背棄耶和華去事奉別的神明, 17因為我們的上帝耶和華曾領我們和我們的祖先脫離埃及人的奴役,在我們眼前行大神蹟,一路保護我們安然經過列邦。 18耶和華把這地方的亞摩利人等外族人從我們面前趕走了,我們必事奉祂,因為祂是我們的上帝。」

19約書亞說:「你們不能事奉耶和華,祂是一位聖潔的上帝,祂痛恨不貞,必不赦免你們的過犯和罪惡。 20如果你們背棄耶和華,去拜外族的神明,儘管祂曾經恩待你們,也必降禍給你們,毀滅你們。」 21民眾答道:「不,我們一定要事奉耶和華。」 22約書亞說:「現在你們自己作證,你們已選擇事奉耶和華。」民眾答道:「我們願意自己作證。」 23約書亞說:「這樣,你們現在就要摒棄你們中間的外族神明,專心歸向以色列的上帝耶和華。」 24民眾答道:「我們必事奉我們的上帝耶和華,聽從祂的話。」 25當天約書亞與民眾立約,在示劍為他們訂立律例和典章。 26約書亞把這些話都寫在上帝的律法書上,又把一塊大石頭豎立在耶和華聖所旁邊的橡樹下。 27然後,他對民眾說:「看啊,這塊石頭可以為我們作證,它聽到了耶和華所吩咐我們的話。如果你們背棄上帝,它必作證。」 28於是,約書亞命民眾各自返回自己的地方。

約書亞去世

29後來,耶和華的僕人、的兒子約書亞去世了,享年一百一十歲。 30以色列人把他葬在他的土地上,就是在迦實山北邊、以法蓮山區的亭拿·西拉

31約書亞在世的時候,以色列人都事奉耶和華。他死後,在那些經歷過耶和華奇妙作為的長老還健在期間,以色列人仍事奉耶和華。

32以色列人把從埃及帶出來的約瑟的骸骨葬在示劍,在從前雅各用一百塊銀子向哈抹的子孫買的那塊地裡。哈抹示劍的父親。後來那塊地成了約瑟子孫的產業。

33亞倫的兒子以利亞撒也死了,他們把他葬在他兒子非尼哈分到的以法蓮山區的基比亞

New Amharic Standard Version

ኢያሱ 24:1-33

ቃል ኪዳኑ በሴኬም ታደሰ

1ከዚያም ኢያሱ የእስራኤልን ነገዶች ሁሉ በሴኬም ሰበሰበ፤ የእስራኤልንም ሽማግሌዎች፣ መሪዎች፣ ፈራጆችና ሹማምት ጠራ፤ እነርሱም በእግዚአብሔር ፊት ቆሙ።

2ኢያሱም ሕዝቡን ሁሉ እንዲህ አላቸው፤ “የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘የቀድሞ አባቶቻችሁ፣ የአብርሃምንና የናኮርን አባት ታራን ጨምሮ ከብዙ ዘመን በፊት ከወንዙ ማዶ ኖሩ24፥2 በዚህ እንዲሁም ቍጥር 3፡14 እና 15 ላይ የተጠቀሰው የኤፍራጥስ ወንዝ ነው።፤ ሌሎችንም አማልክት አመለኩ። 3እኔ ግን አባታችሁን አብርሃምን ከወንዙ ማዶ ካለው ምድር አምጥቼ፣ በከነዓን ምድር ሁሉ መራሁት፤ ዘሮቹን አበዛሁለት፤ ይስሐቅንም ሰጠሁት። 4ለይስሐቅ ያዕቆብንና ዔሳውን ሰጠሁት፤ ለዔሳውም ኰረብታማውን የሴይርን ምድር ርስት አድርጌ ሰጠሁት፤ ያዕቆብና ልጆቹ ግን ወደ ግብፅ ወረዱ።

5“ ‘ከዚያም ሙሴንና አሮንን ላክሁ፤ ባመጣሁት መቅሠፍት ግብፃውያንን አስጨንቄ፣ እናንተን ከዚያ አወጣኋችሁ። 6አባቶቻችሁን ከግብፅ ባወጣኋቸው ጊዜ፣ ወደ ባሕሩ መጣችሁ፤ ግብፃውያንም በሠረገሎችና24፥6 ወይም ሠረገለኞች ተብሎ መተርጐም ይቻላል። በፈረሰኞች እስከ ቀይ ባሕር24፥6 ዕብራይስጡ ያም ሳውፍ ይላል፤ ይኸውም የደንገል ባሕር ማለት ነው። ድረስ ተከታተሏቸው። 7እነርሱ ግን ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤ እርሱም በእናንተና በግብፃውያን መካከል ጨለማ እንዲሆን አደረገ። ባሕሩን በላያቸው አመጣ፤ አሰጠማቸውም። በግብፃውያን ላይ ያደረግሁትንም ራሳችሁ በዐይናችሁ አያችሁ፤ በምድረ በዳም ብዙ ጊዜ ኖራችሁ።

8“ ‘በምሥራቅ ዮርዳኖስ ወደሚኖሩት ወደ አሞራውያን ምድር አመጣኋችሁ፤ እነርሱ ወጓችሁ፤ እኔ ግን አሳልፌ በእጃችሁ ሰጠኋቸው፤ ከፊታችሁ አጠፋኋቸው፤ እናንተም ምድራቸውን ወረሳችሁ። 9የሞዓብ ንጉሥ የሴፎር ልጅ ባላቅ፣ እስራኤልን ለመውጋት ተነሣ፣ እናንተንም መጥቶ ይረግማችሁ ዘንድ ወደ ቢዖር ልጅ ወደ በለዓም መልእክተኛ ላከ፤ 10እኔ ግን በለዓምን ልሰማው አልፈለግሁም፤ ስለዚህ ደግሞ ደጋግሞ መረቃችሁ፤ እኔም፤ ከባላቅ እጅ ታደግኋችሁ።

11“ ‘ከዚያም ዮርዳኖስን ተሻገራችሁ፤ ወደ ኢያሪኮ መጣችሁ፤ አሞራውያን፣ ፌርዛውያን፣ ከነዓናውያን፣ ኬጢያውያን፣ ጌርጌሳውያን፣ ኤዊያውያንና ኢያቡሳውያን እንደ ወጓችሁ ሁሉ፣ የኢያሪኮም ነዋሪዎች ወጓችሁ። 12በፊታችሁ ተርብ ላክሁ፤ ይህም እነርሱንና ሁለቱን የአሞራውያን ነገሥታት ጭምር ከፊታችሁ አሳደደ፤ ይህ ደግሞ በራሳችሁ ሰይፍና ቀስት ያደረጋችሁት አይደለም። 13ስለዚህ ያልደከማችሁበትን ምድርና ያልሠራችኋቸውን ከተሞች ሰጠኋችሁ። እነሆ፣ በከተሞቹ ትኖራላችሁ፤ ካልተከላችሁት የወይን ተክልና የወይራ ዛፍ ትበላላችሁ።’

14“አሁንም እግዚአብሔርን ፍሩ፤ በፍጹም ታማኝነትም ተገዙለት። የቀድሞ አባቶቻችሁ ከወንዙ ማዶና በግብፅ ያመለኳቸውን አማልክት ከእናንተ አርቁ፤ እግዚአብሔርን ብቻ አምልኩ። 15እግዚአብሔርን ማምለክ የማያስፈልግ መስሎ ከታያችሁ ግን፣ የቀድሞ አባቶቻችሁ ከወንዙ ማዶ ካመለኳቸው አማልክት ወይም በምድራቸው የምትኖሩባቸው አሞራውያን ከሚያመልኳቸው አማልክት ታመልኩ እንደ ሆነ የምታመልኩትን ዛሬውኑ ምረጡ፤ እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን።”

16ከዚያም ሕዝቡ እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ሌሎችን አማልእክት ለማምለክ ብለን እግዚአብሔርን መተው ከእኛ ይራቅ። 17እኛንና የቀደሙ አባቶቻችንን ከዚያ ከጦርነት ምድር ከግብፅ ያወጣን፣ በፊታችንም እነዚያን ታላላቅ ምልክቶች ያደረገ ማነው? ራሱ አምላካችን እግዚአብሔር አይደለምን? በጕዟችን ላይና ባለፍንባቸውም ሕዝቦች ሁሉ ዘንድ የጠበቀን እርሱ ነው። 18እንዲሁም እግዚአብሔር በምድሪቱ የሚኖሩትን አሞራውያንን ጨምሮ ሕዝቦችን ሁሉ ከፊታችን አሳደደ፤ ስለዚህ እኛም እግዚአብሔርን እናመልካለን፤ አምላካችን ነውና።”

19ኢያሱም ሕዝቡን እንዲህ አለ፤ “እግዚአብሔርን ማምለክ አትችሉም፤ እርሱ ቅዱስ አምላክና፤ ቀናተኛም አምላክ ነው፤ ዐመፃችሁን ወይም ኀጢአታችሁን ይቅር አይልም። 20እግዚአብሔርን ትታችሁ ባዕዳን አማልክትን የምታመልኩ ከሆነ፣ መልካም ነገር ካደረገላችሁ በኋላ ተመልሶ ክፉ ነገር ያደርግባችኋል፤ ያጠፋችኋልም።”

21ሕዝቡ ግን ኢያሱን፣ “የለም! እኛ እግዚአብሔርን እናመልካለን” አሉት።

22ከዚያም ኢያሱ፣ “እንግዲህ እግዚአብሔርን ለማምለክ መርጣችኋልና በራሳችሁ ላይ ምስክሮች ናችሁ” አላቸው።

እነርሱም፣ “አዎን ምስክሮች ነን” ሲሉ መለሱ።

23ኢያሱም፣ “እንግዲህ በመካከላችሁ ያሉትን ባዕዳን አማልክት አስወግዱ፤ ልባችሁንም ወደ እስራኤል አምላክ ወደ እግዚአብሔር መልሱ” አላቸው።

24ሕዝቡም ኢያሱን፣ “እኛ አምላካችንን እግዚአብሔርን እናመልካለን፤ እንታዘዝለታለንም” አሉት።

25በዚያን ቀን ኢያሱ ከሕዝቡ ጋር ቃል ኪዳን አደረገ፤ የሚመሩበትንም ደንብና ሥርዐት እዚያው ሴኬም ሰጣቸው። 26ኢያሱም እነዚህን ቃሎች በእግዚአብሔር የሕግ መጽሐፍ ጻፋቸው፤ ትልቅ ድንጋይም ወስዶ በባሉጥ ዛፍ ሥር፣ በተቀደሰው በእግዚአብሔር ስፍራ አጠገብ አቆመው።

27ኢያሱም ሕዝቡን ሁሉ፣ “እነሆ፤ ይህ ድንጋይ፣ እግዚአብሔር የተናገረንን ሁሉ ሰምቷል፣ በእኛም ይመሰክርብናል፤ እናንተም በአምላካችሁ ዘንድ እውነተኞች ሆናችሁ ባትገኙ ምስክር ይሆንባችኋል” አላቸው።

ኢያሱ በተሰፋዪቱ ምድር ተቀበረ

24፥29-31 ተጓ ምብ – መሳ 2፥6-9

28ከዚያም ኢያሱ ሕዝቡን ሁሉ ወደየርስቱ እንዲሄድ አሰናበተ።

29ከዚህ በኋላ የእግዚአብሔር ባሪያ የነዌ ልጅ ኢያሱ በመቶ ዐሥር ዓመቱ ሞተ። 30በኰረብታማው በኤፍሬም አገር በምትገኘው፣ ከገዓስ ተራራ በስተ ሰሜን ባለችው በራሱ ርስት በተምናሴራ ቀበሩት።

31ኢያሱ በሕይወት በነበረበት ዘመን ሁሉ፣ ከኢያሱም በኋላ በሕይወት በኖሩትና እግዚአብሔር ለእስራኤል ያደረገውን ሁሉ በሚያውቁት ሽማግሌዎች ዘመን ሁሉ እስራኤላውያን እግዚአብሔርን አመለኩ።

32እስራኤላውያን ከግብፅ ያወጡት የዮሴፍ ዐፅም፣ ያዕቆብ ከሰኬም አባት ከኤሞር በመቶ ሰቅል24፥32 ዕብራይስጡ አንድ መቶ ከሲታሃስ ይላል፤ ክብደቱና ዋጋው በትክክል የማይታወቅ የገንዘብ ዐይነት ነው። ብር በገዛው በሴኬም ምድር ተቀበረ፤ ይህችም የዮሴፍ ዘሮች ርስት ሆነች።

33እንዲሁም የአሮን ልጅ አልዓዛር ሞተ፤ እርሱም በኰረብታማው በኤፍሬም አገር በሚገኘው ለልጁ ለፊንሐስ በዕጣ በደረሰው በጊብዓ ምድር ተቀበረ።