箴言 1 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

箴言 1:1-33

箴言的價值

1這是大衛的兒子以色列所羅門的箴言。

2為使人認識智慧和教誨,

領悟真知灼見;

3為使人接受勸誡,

為人處事仁義、公平、正直;

4使愚昧人明智,

使青年有知識和明辨力;

5使智者聽了長學問,

明哲聽了得指引;

6使人領悟箴言和比喻,

明白智者的話和謎語。

7知識始於敬畏耶和華,

愚人輕視智慧和教誨。

8孩子啊,

你要聽從父親的教誨,

不可背棄母親的訓言。

9因為這要作你頭上的華冠,

頸上的項鏈。

10孩子啊,惡人若引誘你,

千萬不要聽從。

11他們若說:「跟我們來吧,

我們去埋伏殺人,

暗害無辜者取樂;

12我們要像陰間一樣生吞他們,

整個吞沒他們,

使他們如墜入墳墓的人;

13我們必得到各樣寶物,

把戰利品裝滿我們的房屋。

14跟我們一起幹吧,

大家有福同享!」

15孩子啊,

不要走他們的道,

切莫行他們的路。

16因為他們奔向罪惡,

急速地去殺人流血。

17在飛鳥眼前設網羅,徒勞無功。

18他們埋伏,卻自流己血;

他們伏擊,卻自害己命。

19這就是貪愛不義之財者的結局,

不義之財終要奪去他們的性命。

智慧的勸誡

20智慧在大街上高喊,

在廣場上揚聲,

21在熱鬧的市集宣告,

在城門口演說:

22「你們愚昧人喜愛愚昧,

嘲諷者以嘲弄為樂,

無知者厭惡知識,

要到什麼時候呢?

23你們若因我的責備而回轉,

我就向你們顯明我的旨意1·23 我就向你們顯明我的旨意」希伯來文是「我就將我的靈澆灌你們」。

叫你們明白我的話語。

24我呼喚你們,

你們卻充耳不聞;

我向你們招手,

你們卻視若無睹。

25你們漠視我的勸誡,

不接受我的責備。

26因此,

你們遭遇災難時,

我必發笑;

驚恐臨到你們時,

我必嗤笑——

27那時,恐懼如風暴襲擊你們,

災難如旋風臨到你們,

憂愁和苦難吞沒你們。

28你們呼求我,

我也不回答;

你們懇切地尋找我,

卻找不到。

29因為你們厭惡知識,

不願意敬畏耶和華,

30不接受我的勸誡,

又藐視我的責備。

31所以,你們必自食其果,

因自己的惡謀而吃盡苦頭。

32愚昧人背離正道,

自招滅亡;

愚頑人逍遙自在,

毀掉自己。

33然而,那聽從我的必安然居住,

得享安寧,

不怕災禍。」

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 1:1-33

መግቢያ፤ የምሳሌዎቹ ዐላማና ጭብጥ

1የእስራኤል ንጉሥ፣ የዳዊት ልጅ የሰሎሞን ምሳሌዎች፤

2ጥበብንና ተግሣጽን ለመቀበል፤

ጥልቅ ሐሳብ የሚገልጡ ቃላትን ለማስተዋል፤

3ጽድቅን፣ ፍትሕንና ሚዛናዊ ብያኔን በማድረግ፣

የተገራ ጠቢብ ልቦናን ለማግኘት፤

4ብስለት ለሌላቸው አስተዋይነትን፣

በዕድሜ ለጋ ለሆኑት ዕውቀትንና ልባምነትን ለመስጠት፤

5ጥበበኞች ያድምጡ፤ ትምህርታቸውንም ያዳብሩ፤

አስተዋዮችም መመሪያ ያግኙበት፤

6ይህም የጠቢባንን ምሳሌዎችና ተምሳሌቶች፣

አባባሎችና ዕንቈቅልሾች ይረዱ ዘንድ ነው።

7እግዚአብሔርን መፍራት የዕውቀት መጀመሪያ ነው፤

ተላሎች1፥7 በመጽሐፈ ምሳሌና በብሉይ ኪዳን ሌሎች መጻሕፍት ውስጥ ተላላ የሚለው በተደጋጋሚ ተጽፏል፤ ይህም የሞራል ጕድለትን ያመለክታል። ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ።

ጥበብን ገንዘብ ለማድረግ የተሰጠ ምክር

8ልጄ ሆይ፤ የአባትህን ምክር አድምጥ፤

የእናትህንም ትምህርት አትተው።

9ለራስህ ሞገስን የሚያጐናጽፍ አክሊል፣

ዐንገትህን የሚያስውብ ድሪ ይሆንልሃል።

10ልጄ ሆይ፤ ኀጢአተኞች ቢያባብሉህ፣

እሺ አትበላቸው፤

11“ከእኛ ጋር ናና፣ ደም ለማፍሰስ እናድባ፤

በደል በሌለበት ሰው ላይ እንሸምቅ፤

12እንደ መቃብር፣ ወደ ጕድጓድ1፥12 በዕብራይስጡ ሲኦል ይላል። እንደሚወርዱ፣

ከነሕይወታቸው እንዳሉ እንዋጣቸው፤

13ውድ የሆኑ ነገሮችን ሁሉ በየዐይነቱ እናገኛለን፤

ቤቶቻችንንም በዝርፊያ እንሞላለን፤

14ከእኛ ጋር ዕጣህን ጣል፤

የጋራ ቦርሳ ይኖረናል” ቢሉህ፣

15ልጄ ሆይ፤ አብረሃቸው አትሂድ፤

በሚሄዱበትም መንገድ እግርህን አታንሣ፤

16እግራቸው ወደ ኀጢአት ይቸኵላል፤

ደም ለማፍሰስም ፈጣኖች ናቸው።

17ወፎች ፊት እያዩ ወጥመድ መዘርጋት፣

ምንኛ ከንቱ ነው!

18እነዚህ ሰዎች የሚያደቡት በገዛ ደማቸው ላይ ነው፤

የሚሸምቁትም በራሳቸው ላይ ብቻ ነው።

19ያላግባብ ለጥቅም የሚሯሯጡ ሁሉ መጨረሻቸው እንዲህ ነው፤

የሕይወታቸው መጥፊያም ይኸው ነው።

ጥበብን ለሚያናንቁ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

20ጥበብ በጐዳና ላይ ጮኻ ትጣራለች፤

በየአደባባዩ ድምፅዋን ከፍ ታደርጋለች፤

21ዉካታ በበዛባቸው ጐዳናዎች ላይ1፥21 በዕብራይስጡና በሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች በቅጥሮች ጫፍ ላይ ይላሉ። ትጮኻለች፤

በከተማዪቱም መግቢያ በር ላይ እንዲህ ትላለች፤

22“እናንት ብስለት የሌላችሁ1፥22 በዕብራይስጡ ብስለት የሌለው የሚለው ቃል በዚህ መጽሐፍ በአጠቃላይ መልካም ምግባር የሌለውንና ክፋትን ለማድረግ ልቡ ያዘነበለ ሰውን ያመለክታል። ማስተዋል የሌለበት መንገዳችሁን እስከ መቼ ትወዱታላችሁ?

ፌዘኞች በፌዝ ደስ የሚሰኙት፣

ሞኞችስ ዕውቀትን የሚጠሉት እስከ መቼ ነው?

23ዘለፋዬን ብትሰሙኝ ኖሮ፣

ልቤን ባፈሰስሁላችሁ፣

ሐሳቤንም ባሳወቅኋችሁ ነበር።

24ነገር ግን በተጣራሁ ጊዜ እንቢ ስላላችሁኝ፣

እጄንም ስዘረጋ ማንም ግድ ስላልነበረው፣

25ምክሬን ሁሉ ስለ ናቃችሁ፣

ዘለፋዬንም ስላልተቀበላችሁ፣

26እኔ ደግሞ በመከራችሁ እሥቅባችኋለሁ፤

መዓት በሚወርድባችሁም ጊዜ አፌዝባችኋለሁ፤

27መዓት እንደ ማዕበል ሲያናውጣችሁ፣

መከራም እንደ ዐውሎ ነፋስ ሲጠራርጋችሁ፣

ሥቃይና ችግር ሲያጥለቀልቃችሁ አፌዝባችኋለሁ።

28“በዚያን ጊዜ ይጠሩኛል፤ እኔ ግን አልመልስላቸውም፤

አጥብቀው ይፈልጉኛል፤ ነገር ግን አያገኙኝም።

29ዕውቀትን ስለ ጠሉ፣

እግዚአብሔርንም መፍራት ስላልመረጡ፣

30ምክሬን ለመቀበል ስላልፈለጉ፣

ዘለፋዬን ስለ ናቁ፣

31የመንገዳቸውን ፍሬ ይበላሉ፤

የዕቅዳቸውንም ውጤት ይጠግባሉ።

32ብስለት የሌላቸውን ስድነታቸው ይገድላቸዋል፤

ተላሎችንም ቸልተኝነታቸው ያጠፋቸዋል፤

33የሚያዳምጠኝ ሁሉ ግን በሰላም ይኖራል፤

ክፉን ሳይፈራ ያለ ሥጋት ይቀመጣል።”