哈巴谷書 3 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

哈巴谷書 3:1-19

哈巴谷的禱告

1以下是哈巴谷先知的禱告,採用流離調3·1 流離調是希伯來詩歌的一種曲調。

2耶和華啊,我聽過你的威名;

耶和華啊,我對你的作為充滿敬畏。

求你如今再次彰顯你的作為,

求你發怒的時候仍以憐憫為念。

3上帝從提幔來,

聖者從巴蘭山來。(細拉)

祂的榮耀遮蔽諸天,

頌讚祂的聲音響徹大地。

4祂的榮光猶如太陽的光輝,

祂的手射出光芒,

其中蘊藏著大能。

5瘟疫行在祂前面,

災病跟在祂腳後。

6祂停下,大地就震動;

祂觀看,萬民就戰慄。

古老的山嶽崩裂,

遠古的丘陵塌陷,

但祂的作為永遠不變。

7我看見古珊的帳篷遭難,

米甸人的幔子顫抖。

8耶和華啊,你是向江河發怒嗎?

你乘著得勝的戰車而來,

是向江河生氣嗎?

是向海洋發怒嗎?

9你拿出弓,要射出許多箭羽。(細拉)

你以江河分開大地。

10群山看見你就戰慄,

大雨傾盆,

深淵翻騰,波浪滔天。

11你射出的箭閃閃發光,

你的槍熠熠生輝,

以致日月都停在天上。

12你懷著烈怒走遍大地,

踐踏萬國。

13你出來是為了拯救你的子民,

拯救你膏立的王。

你打垮邪惡之人的首領,

從頭到腳徹底毀滅他們。(細拉)

14他們的軍隊如旋風而至,

要驅散我們,

他們以暗中吞噬貧民為樂,

但你用他們的矛刺透他們的頭顱。

15你騎馬踐踏洶湧的大海。

16我聽到這些,

就膽戰心驚,嘴唇哆嗦,

四肢無力,雙腿發抖。

但我仍要靜候災難臨到入侵者的日子。

17即使無花果樹不發芽,

葡萄樹不結果,

橄欖樹無收成,

田地不產糧,

圈裡沒有羊,

棚裡沒有牛,

18我仍要因耶和華而歡欣,

因拯救我的上帝而喜樂。

19主耶和華是我的力量,

祂使我的腳如母鹿的蹄,

穩行在高處。

這首歌交給樂長,用弦樂器伴奏。

New Amharic Standard Version

ዕንባቆም 3:1-19

የዕንባቆም ጸሎት

1በዝማሬ የቀረበ የነቢዩ የዕንባቆም ጸሎት፤ በሺግዮኖት።3፥1 የሥነ ጽሑፍ ወይም የሙዚቃ ቋንቋ ሳይሆን አይቀርም።

2እግዚአብሔር ሆይ፤ ዝናህን ሰምቻለሁ፤

እግዚአብሔር ሆይ፤ ሥራህም አስፈራኝ፤

በእኛ ዘመን አድሳቸው፤

በእኛም ጊዜ እንዲታወቁ አድርግ፤

በመዓት ጊዜ ምሕረትን ዐስብ።

3እግዚአብሔር ከቴማን፣

ቅዱሱም ከፋራን ተራራ መጣ። ሴላ3፥3 ትርጕሙ በትክክል የማይታወቅ ቢሆንም የዜማ ቃል ሳይሆን አይቀርም።

ክብሩ ሰማያትን ሸፈነ፤

ውዳሴውም ምድርን ሞላ።

4ጸዳሉ እንደ ፀሓይ ብርሃን ነው፤

ጨረር ከእጁ ወጣ፤

ኀይሉም በዚያ ተሰውሯል።

5መቅሠፍት በፊቱ ሄደ፤

ቸነፈርም እግር በእግር ተከተለው።

6ቆመ፤ ምድርን አንቀጠቀጠ፤

ተመለከተ፤ ሕዝቦችን አብረከረከ፤

የዘላለም ተራሮች ተፈረካከሱ፤

የጥንት ኰረብቶችም ፈራረሱ፤

መንገዱ ዘላለማዊ ነው።

7የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ፣

የምድያምም መኖሪያዎች ሲታወኩ አየሁ።

8እግዚአብሔር ሆይ፤ በወንዞች ላይ ተቈጣህን?

መዓትህስ በምንጮች ላይ ነበርን?

በፈረሶችህና በድል አድራጊ ሠረገሎችህ

በጋለብህ ጊዜ፣

በባሕር ላይ ተቈጥተህ ነበርን?

9ቀስትህን አዘጋጀህ፤

ፍላጻም እንዲመጣልህ አዘዝህ፤ ሴላ

ምድርን በወንዞች ከፈልህ፤

10ተራሮች አዩህ፤ ተጨነቁም፤

የውሃ ሞገድ ዐልፎ ሄደ፤

ቀላዩ ደነፋ፤

ማዕበሉንም ወደ ላይ አነሣ።

11ከሚወረወሩ ፍላጾችህ፣

ከሚያብረቀርቅ የጦርህ ነጸብራቅ የተነሣም፣

ፀሓይና ጨረቃ በቦታቸው ቆሙ።

12በምድር ላይ በመዓት ተመላለስህ፤

ሕዝቦችንም በቍጣ ረገጥሃቸው።

13ሕዝብህን ለመታደግ፣

የቀባኸውንም ለማዳን ወጣህ፤

የክፋትን ምድር መሪ ቀጠቀጥህ፤

ከራስ ጠጕሩ እስከ እግር ጥፍሩም ዕርቃኑን አስቀረኸው። ሴላ

14እንደ ዐውሎ ነፋስ ሊበታትነን የመጣውን፣

ምስኪኑን በስውር በመዋጥ የሚደሰተውን፣

የሰራዊት አለቃ ራስ፣

በገዛ ጦሩ ወጋህ።

15ታላላቅ ውሆችን በመናጥ፣

ባሕሩን በፈረሶችህ ረገጥህ።

16እኔ ሰማሁ፤ ልቤም ደነገጠብኝ፤

ከንፈሬ ከድምፁ የተነሣ ተንቀጠቀጠ፤

ፍርሀት እስከ ዐጥንቴ ዘልቆ ገባ፤

እግሬም ተብረከረከ፤

ሆኖም በሚወርረን ሕዝብ ላይ እስኪመጣ ድረስ፣

የጥፋትን ቀን በትዕግሥት እጠባበቃለሁ።

17ምንም እንኳ የበለስ ዛፍ ባያፈራ፣

ከወይን ተክልም ፍሬ ባይገኝ፣

የወይራም ዛፍ ፍሬ ባይሰጥ፣

ዕርሻዎችም ሰብል ባይሰጡ፣

የበጎች ጕረኖ እንኳ ባዶውን ቢቀር፣

ላሞችም በበረት ውስጥ ባይገኙ፣

18እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤

በድነቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ።

19ጌታ እግዚአብሔር ኀይሌ ነው፤

እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤

በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል።

ለመዘምራን አለቃ፣ በባለ አውታር መሣሪያዎቼ የተዘመረ መዝሙር።