西番雅書 1 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

西番雅書 1:1-18

1猶大亞們的兒子約西亞執政期間,耶和華對希西迦的玄孫、亞瑪利亞的曾孫、基大利的孫子、古示的兒子西番雅說:

耶和華審判的日子

2「我必毀滅地上的一切。

這是耶和華說的。

3我必毀滅人類、獸類、

天上的鳥和海裡的魚。

我必使惡人倒斃,

我必剷除地上的人類。

這是耶和華說的。

4「我必伸手攻擊猶大

以及所有住在耶路撒冷的人,

剷除巴力的餘跡及拜偶像之祭司的名號。

5我必剷除那些在屋頂祭拜天上萬象的人,

剷除敬拜我、憑我起誓又憑米勒公起誓的人,

6剷除離棄我、不尋求我、不求問我的人。」

7要在主耶和華面前肅靜,

因為耶和華的日子近了。

耶和華已準備好祭物,

潔淨了祂邀請的人。

8耶和華說:「在我獻祭的日子,

我必懲罰首領和王子,

以及所有穿外族服裝的人。

9到那日,我必懲罰所有跳過門檻1·9 跳過門檻……的人」指祭拜偶像的人,參見撒母耳記上5·5

使主人的家充滿暴力和欺詐的人。

10到那日,魚門必傳出哭喊聲,

新區必響起哀號聲,

山陵必發出崩裂的巨響。

這是耶和華說的。

11市場區的居民啊,哀哭吧!

因為所有的商人必滅亡,

所有做買賣的必被剷除。

12那時,我必提著燈巡查耶路撒冷

懲罰那些安於罪中的人。

他們心想,『耶和華不賜福也不降禍。』

13他們的財物必遭搶掠,

家園必淪為廢墟。

他們建造房屋,卻不能住在裡面;

栽種葡萄園,卻喝不到葡萄酒。

14「耶和華的大日子近了,

近了,很快就到了。

那將是痛苦的日子,

勇士也必淒聲哀號。

15那是降烈怒的日子,

是困苦艱難的日子,

是摧殘毀壞的日子,

是黑暗幽冥的日子,

是陰霾密佈的日子,

16是吹號呐喊、

攻打堅城高壘的日子。

17「我要使人們災難臨頭,

以致他們行路像瞎子,

因為他們得罪了我。

他們的血必被倒出,如同灰塵;

他們的屍體必被丟棄,如同糞便。

18在耶和華發怒的日子,

他們的金銀救不了他們。

祂的怒火必吞噬大地,

祂必驟然毀滅一切世人。」

New Amharic Standard Version

ሶፎንያስ 1:1-18

1በይሁዳ ንጉሥ በአሞጽ ልጅ በኢዮስያስ ዘመን ወደ ሕዝቅያስ ልጅ፣ ወደ አማርያ ልጅ፣ ወደ ጎዶልያስ ልጅ፣ ወደ ኵሲ ልጅ ወደ ሶፎንያስ የመጣ የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው፤

ስለሚመጣው ጥፋት የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

2“ማንኛውንም ነገር፣

ከምድር ገጽ አጠፋለሁ”

ይላል እግዚአብሔር

3“ሰውንና እንስሳን አጠፋለሁ፤

የሰማይን ወፎች፣

የባሕርንም ዓሦች አጠፋለሁ፤

ሰውን ከምድር ገጽ በማስወግድበት ጊዜ፣

ክፉዎች የፍርስራሽ1፥3 የዕብራይስጡ ቃል ትርጕም በትክክል አይታወቅም። ክምር ይሆናሉ”

ይላል እግዚአብሔር

በይሁዳ ላይ የተነገረ ጥፋት

4“እጄን በይሁዳ፣

በኢየሩሳሌምም በሚኖሩት ሁሉ ላይ አነሣለሁ፤

የበኣልን ትሩፍ፣

የጣዖታቱንና የአመንዝራ ካህናቱን ስም ሁሉ ከዚህ ስፍራ አጠፋለሁ፤

5የሰማይን ሰራዊት ለማምለክ፣

በሰገነት ላይ ወጥተው የሚሰግዱትን፣

ለእግዚአብሔር እየሰገዱ፣ በስሙም እየማሉ፣

በሚልኮምም1፥5 በዕብራይስጥ ማልካም ይባላል። ደግሞ የሚምሉትን፣

6እግዚአብሔርን ከመከተል ወደ ኋላ የሚመለሱትን፣

እግዚአብሔርን የማይፈልጉትን፣ እንዲረዳቸውም የማይጠይቁትን አጠፋለሁ።”

7በጌታ እግዚአብሔር ፊት ዝም በሉ፤

የእግዚአብሔር ቀን ቀርቧልና።

እግዚአብሔር መሥዋዕት አዘጋጅቷል፤

የጠራቸውንም ቀድሷል።

8በእግዚአብሔር የመሥዋዕት ቀን፣

መሳፍንቱንና የንጉሡን ልጆች፣

እንግዳ ልብስ የሚለብሱትን ሁሉ እቀጣለሁ።

9በዚያን ቀን፣

በመድረኩ ላይ የሚዘልሉትን ሁሉ፣

የአማልክታቸውን ቤት፣

በዐመፅና በማጭበርበር የሚሞሉትን እቀጣለሁ።

10እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

“በዚያ ቀን ‘ከዓሣ በር’ ጩኸት

በሁለተኛው አደባባይ ዋይታ፣

ከኰረብቶችም ታላቅ ሽብር ይሰማል።

11እናንት በመክቴሽ1፥11 አንዳንዶች በሞርታር ይላሉ። ገበያ የምትኖሩ ዋይ በሉ፤

ነጋዴዎቻችሁ ሁሉ ይደመሰሳሉ፤

በብር የሚነግዱትም ሁሉ ይሞታሉ።

12በዚያ ዘመን ኢየሩሳሌምን በመብራት እፈትሻለሁ፤

ተንደላቅቀው የሚኖሩትን፣

በዝቃጩ ላይ እንደ ቀረ የወይን ጠጅ የሆኑትን፣

‘ክፉም ይሁን መልካም፣

እግዚአብሔር ምንም አያደርግም’ የሚሉትን ቸልተኞች እቀጣለሁ።

13ሀብታቸው ይዘረፋል፤

ቤታቸው ይፈራርሳል፤

ቤቶች ይሠራሉ፤

ነገር ግን አይኖሩባቸውም፤

ወይን ይተክላሉ፤

ጠጁን ግን አይጠጡም።”

ታላቁ የእግዚአብሔር ቀን

14“ታላቁ የእግዚአብሔር ቀን ቅርብ ነው፤

ቅርብ ነው ፈጥኖም ይመጣል፤

በእግዚአብሔር ቀን የሚሰማው ልቅሶ መራራ ነው፤

በዚያ ጦረኛውም ምርር ብሎ ይጮኻል፤

15ያ ቀን የመዓት ቀን፣

የመከራና የጭንቀት ቀን፣

የሁከትና የጥፋት ቀን፣

የጨለማና የጭጋግ ቀን፣

የደመናና የድቅድቅ ጨለማ ቀን ይሆናል፤

16ያ ቀን በተመሸጉ ከተሞችና፣

በረዣዥም ግንቦች ላይ፣

የመለከት ድምፅና የጦርነት ጩኸት የሚሰማበት ቀን ይሆናል።

17“እንደ ዕውር እንዲራመዱ፣

በሰዎች ላይ ጭንቀት አመጣባቸዋለሁ፤

በእግዚአብሔር ላይ ኀጢአትን ሠርተዋልና።

ደማቸው እንደ ትቢያ፣

ሥጋቸውም እንደ ጕድፍ ይጣላል።

18በእግዚአብሔር የቍጣ ቀን፣

ብራቸውም ሆነ ወርቃቸው

ሊያድናቸው አይችልም።”

መላዪቱ ምድር፣

በቅናቱ ትበላለች፤

በምድር በሚኖሩ ሁሉ ላይ፣

ድንገተኛ ፍጻሜ ያመጣባቸዋልና።