列王紀下 3 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

列王紀下 3:1-27

以色列與摩押爭戰

1猶大約沙法執政第十八年,亞哈的兒子約蘭撒瑪利亞登基做以色列王,執政十二年。 2他做耶和華視為惡的事,不過沒有他父母那麼敗壞,因為他除掉了他父親立的巴力神柱。 3可是他沉溺於尼八的兒子耶羅波安所犯的罪惡,使以色列人陷入罪中。

4摩押米沙以牧羊為業,每年向以色列王進貢十萬隻公綿羊的羊毛和十萬隻羊羔。 5亞哈死後,米沙背叛了以色列王。 6那時,約蘭撒瑪利亞出發,召集以色列全軍。 7他還派人去對猶大約沙法說:「摩押王背叛了我,你肯和我一起去攻打摩押嗎?」約沙法回覆說:「我肯去。你我不分彼此,我的軍隊就是你的軍隊,我的戰馬就是你的戰馬。 8我們從哪一條路進攻呢?」約蘭答道:「從以東的曠野。」

9於是,以色列王跟猶大王和以東王聯合出兵。他們繞道行了七天,軍隊和隨行的牲畜都沒有水喝了。 10以色列王叫道:「唉!怎麼辦呢?耶和華招聚我們三王,是要把我們交給摩押王!」 11約沙法說:「這裡有沒有耶和華的先知?我們可以託他求問耶和華。」以色列王的一個臣僕答道:「沙法的兒子以利沙在這裡,以前他是以利亞的助手。」 12約沙法說:「耶和華會藉他說話。」於是以色列王、猶大王和以東王一起去見以利沙

13以利沙以色列王說:「我與你有什麼關係?你去問你父母的先知吧!」以色列王說:「不要這樣說,耶和華招聚我們三王,是要把我們交給摩押王!」 14以利沙說:「我事奉的是永活的萬軍之耶和華,我憑祂起誓,若不是看猶大約沙法的情面,我決不理你,也不會見你。 15現在你們給我找一個琴師來。」琴師彈琴的時候,耶和華的靈降在以利沙身上, 16他說:「耶和華吩咐你們要在這山谷中到處挖溝, 17因為耶和華說,『你們雖不見風,也不見雨,但這谷中必到處有水,人畜都會有水喝。』 18這對耶和華來說是微不足道的事,祂還要把摩押人交在你們手中。 19你們必攻陷所有的堅城重鎮,砍倒各種佳美的樹木,堵塞所有水泉,用石頭毀壞一切良田。」 20次日早晨,約在獻祭的時候,水從以東流來,遍地都是水。

21摩押人聽說三王聯軍進攻他們,於是把凡能打仗的,不論老少都聚集起來,把守在邊界上。 22第二天早晨,日光照在水面上,摩押人起來後,看見對面的水像血一樣紅, 23便說:「那是血啊!一定是三王內訌,自相殘殺。弟兄們,我們去搶財物吧!」 24他們到了以色列營,以色列人奮起迎戰,殺得他們轉身逃跑。以色列人乘勝追擊,殺入摩押境內,擊殺摩押人, 25摧毀城邑,人人拋擲石頭填滿所有良田,堵塞一切水泉,砍倒各種佳美樹木。摩押境內僅剩的吉珥·哈列設城也遭到甩石的士兵圍攻。 26摩押王見戰事不利,就率領七百名刀兵,企圖從以東王那邊突圍,但沒有成功。 27於是,他在城上將本應繼承自己王位的長子殺掉,獻為燔祭。以色列人感到非常恐懼3·27 非常恐懼」希伯來文是「大怒」,含「噁心、恐懼」之意。,便退兵回國了。

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 3:1-27

ሞዓብ ዐመፀ

1የይሁዳ ንጉሥ ኢዮሣፍጥ በነገሠ በዐሥራ ስምንተኛው ዓመት፣ የአክአብ ልጅ ኢዮራም በእስራኤል ላይ በሰማርያ ነገሠ፤ ዐሥራ ሁለት ዓመትም ገዛ። 2እርሱም በእግዚአብሔር ፊት የተጠላ ክፉ ድርጊት ፈጸመ፤ ክፉ ድርጊቱ ግን አባትና እናቱ እንደ ፈጸሙት ዐይነት አልነበረም፤ አባቱ ያሠራውንም የበኣልን ሐውልት አስወገደ። 3ነገር ግን የናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም እስራኤልን ባሳተበት ኀጢአት ተያዘ፤ ከዚያም አልተላቀቀም።

4በዚህ ጊዜ የሞዓብ ንጉሥ ሞሳ በግ ያረባ ነበር፤ እርሱም መቶ ሺሕ ጠቦትና የመቶ ሺሕ አውራ በግ ጠጕር ለእስራኤል ንጉሥ ይገብር ነበር። 5አክዓብ ከሞተ በኋላ ግን የሞዓብ ንጉሥ በእስራኤል ንጉሥ ላይ ዐመፀ። 6ስለዚህ በዚያኑ ጊዜ ንጉሥ ኢዮራም ከሰማርያ ተነሥቶ በመሄድ እስራኤልን ሁሉ አሰባሰበ። 7ለይሁዳ ንጉሥ ለኢዮሣፍጥ፣ “የሞዓብ ንጉሥ ስለ ዐመፀብኝ አብረኸኝ ትዘምታለህን?” ሲል መልእክት ላከበት።

እርሱም፣ “አዎን አብሬህ እዘምታለሁ፤ እኔ እንደ አንተው ነኝ፤ ሕዝቤ እንደ ሕዝብህ፤ ፈረሶቼም እንደ ፈረሶችህ ናቸው” በማለት መለሰለት።

8ኢዮሣፍጥም፣ “የምንዘምተው በየትኛው መንገድ ነው” ብሎ ጠየቀው፤

ኢዮራምም “በኤዶም ምድረ በዳ ዐልፈን ነው” ሲል መለሰለት።

9ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥ ከይሁዳ ንጉሥና ከኤዶም ንጉሥ ጋር ለመዝመት ተነሣ። ሰባት ቀን ከዞሩም በኋላ ለሰራዊቱም ሆነ ለእንስሶቻቸው የተረፈ ውሃ አልነበረም።

10የእስራኤልም ንጉሥ፣ “ወዮ! እግዚአብሔር እኛን ሦስት ነገሥታት የጠራን ለሞዓብ አሳልፎ ሊሰጠን ነውን?” አለ።

11ኢዮሣፍጥ ግን፣ “በእርሱ አማካይነት እግዚአብሔርን ለመጠየቅ እንድንችል፣ የእግዚአብሔር ነቢይ እዚህ የለምን?” በማለት ጠየቀ።

ከእስራኤል ንጉሥ የጦር አለቆችም አንዱ፣ “ቀድሞ የኤልያስን እጅ ያስታጥብ የነበረው፤3፥11 የኤልያስ አገልጋይ ነው። የሣፋጥ ልጅ ኤልሳዕ በዚህ አለ” ብሎ መለሰለት።

12ኢዮሣፍጥም፣ “የእግዚአብሔር ቃል ከእርሱ ዘንድ ይገኛል” አለ፤ ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥ፣ ኢዮሣፍጥና የኤዶም ንጉሥ አብረው ወደ እርሱ ወረዱ።

13ኤልሳዕም የእስራኤልን ንጉሥ፤ “ከአንተ ጋር ምን የሚያገናኘን ጕዳይ አለና መጣህ፤ አሁን የአባትህና የእናትህ ነቢያት ወዳሉበት ሂድ” አለው።

የእስራኤልም ንጉሥ መልሶ፣ “ይህማ አይሆንም፤ በሞዓብ እጅ አሳልፎ ሊሰጠን እኛን ሦስት ነገሥታት አንድ ላይ የጠራን እግዚአብሔር ነው” አለ።

14ኤልሳዕም እንዲህ አለው፤ “የማገለግለው ሕያው እግዚአብሔርን፣ የይሁዳን ንጉሥ ኢዮሣፍጥን ባላከብር ኖሮ፣ አንተን አላይም ወይም ጕዳዬ አልልህም ነበር። 15አሁንም ባለ በገና አምጡልኝ።”

ታዲያ ባለ በገናው በሚደረድርበት ጊዜ፣ የእግዚአብሔር እጅ በኤልሳዕ ላይ መጣ፤ 16እንዲህም አለ፤ “እግዚአብሔር የሚለው እንዲህ ነው፤ ‘በዚህ ሸለቆ ብዙ ጕድጓዶች ቈፍሩ።’ 17እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ ‘ነፋስም ሆነ ዝናብ አታዩም፤ ሸለቆው ግን በውሃ ይሞላል፤ እናንተ፣ የቀንድ ከብቶቻችሁና ሌሎች እንስሶቻችሁም ትጠጣላችሁ።’ 18ይህ በእግዚአብሔር ፊት ቀላል ነገር ነው። ሞዓብንም በእጃችሁ አሳልፎ ይሰጣችኋል።

19“የተመሸጉትን ከተሞችና ያማሩትን ከተሞቻቸውን ሁሉ ድል ታደርጋላችሁ። ውብ ዛፎቻቸውን ሁሉ ትቈርጣላችሁ፤ ምንጮቻቸውን በሙሉ ትደፍናላችሁ፤ መልካሙንም ዕርሻ በድንጋይ ታበላሹታላችሁ።”

20በማግስቱም መሥዋዕት በሚቀርብበት ጊዜ፣ እነሆ፤ ከኤዶም በኩል ውሃ እየጐረፈ መጣ፤ ምድሪቱም ውሃ በውሃ ሆነች።

21በዚህ ጊዜ ነገሥታቱ ሊወጓቸው መምጣታቸውን ሞዓባውያን ሁሉ ሰምተው ነበርና፣ ልጅም ሆነ ሽማግሌ፣ መሣሪያ መያዝ የቻለ ሁሉ ተጠርቶ በመውጣት በጠረፉ ላይ ይጠባበቅ ጀመር። 22በማግስቱም ጧት ማልደው ሲነሡም፣ ፀሓይ በውሃው ላይ ታንጸባርቅ ነበር። ማዶ ላሉት ሞዓባውያንም፣ ውሃው እንደ ደም ቀልቶ ታያቸው። 23ስለዚህ፣ “ያ እኮ ደም ነው! ያለ ጥርጥር ነገሥታቱ እርስ በርስ ተዋግተው ተራርደዋል። እንግዲህ ሞዓብ ወደ ምርኮህ ዙር!” ተባባሉ።

24ሞዓባውያን ወደ እስራኤል ሰፈር ሲወጡም፣ እስራኤላውያን ተነሥተው ወጓቸው፤ ሞዓባውያንም ከፊታቸው ሸሹ። ከዚያም እስራኤላውያን ምድሪቱን ወርረው ሞዓባውያንን ፈጇቸው። 25ከተሞቹን ደመሰሱ፤ መልካሙን የዕርሻ መሬት ሁሉ እስኪሸፍነው ድረስ፣ እያንዳንዱ ሰው አንዳንድ ድንጋይ ጣለበት፤ ምንጮቹን በሙሉ ደፈኑ፤ ጥሩ ጥሩውንም ዛፍ ሁሉ ቈርጠው ጣሉ። ቂርሐራሴት ብቻ ከነድንጋይዋ ቀርታ ነበር፤ እርሷንም ቢሆን ባለ ወንጭፉ ሰራዊት ከብቦ አደጋ ጣለባት።

26የሞዓባውያን ንጉሥ በጦርነቱ መሸነፉን እንዳወቀ፣ ሰይፍ የታጠቁ ሰባት መቶ ሰዎች ይዞ የኤዶም ንጉሥ ወዳለበት ጥሶ ለመግባት ሞከረ፤ ነገር ግን አልተሳካላቸውም። 27ከዚያም በእግሩ ተተክቶ የሚነግሠውን፣ የበኵር ልጁን ወስዶ በከተማዪቱ ቅጥር ላይ የሚቃጠል መሥዋዕት አድርጎ አቀረበው። በእስራኤልም ላይ ታላቅ ቍጣ ሆነ፤ ከዚያም ለቅቀው ወደ ገዛ ምድራቸው ተመለሱ።