诗篇 37 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 37:1-40

第 37 篇

义人和恶人的结局

大卫的诗。

1不要因为恶人而烦恼,

也不要羡慕作恶之人,

2因为他们如瞬息枯萎的草芥,

又如转眼消逝的绿草。

3要信靠耶和华,要行善,

要在这片土地上安然度日。

4要以耶和华为乐,

祂必成全你的愿望。

5要把一切交托给耶和华,

信靠祂,祂必帮助你,

6使你的公义如晨光照耀,

你的仁义如日中天。

7要在耶和华面前安静,

耐心等候祂,

不要因恶人道路通达、阴谋得逞而愤愤不平。

8你要抑制怒气,除掉愤怒;

不要心怀不平,

那会导致你作恶。

9因为作恶的终必灭亡,

但等候耶和华的必承受土地。

10再过片刻,恶人必不复存在,

无处可寻。

11但谦卑人必承受土地,

得享太平。

12恶人谋害义人,

对他们咬牙切齿。

13但耶和华嗤笑邪恶人,

因为祂知道他们末日将临。

14恶人拔剑张弓要消灭穷苦人,

杀戮正直人,

15但他们的剑必刺穿自己的心,

他们的弓必被折断。

16义人淡泊一生强过恶人财富如山。

17因为恶人的势力终必瓦解,

耶和华必扶持义人。

18耶和华天天看顾纯全无过的人,

他们的产业永远长存。

19他们在灾难中不致绝望,

在饥荒时仍得饱足。

20但恶人必灭亡,

上帝的仇敌必像野地枯萎的花草,

消逝如烟。

21恶人借债不还,

义人慷慨给予。

22蒙耶和华赐福的人必承受土地,

被耶和华咒诅的人必遭铲除。

23耶和华引领义人的脚步,

喜悦他们所走的路。

24他们即使失脚,也不会跌倒,

因为耶和华的手扶持他们。

25从幼年到老年,

我从未见过义人遭弃,

也未见其后人讨饭。

26他们乐善好施,

后代都蒙祝福。

27你要离恶行善,

就必永远安居。

28因为耶和华喜爱正义,

不丢弃信靠祂的人,

永远保护他们。

恶人的后代必被铲除。

29义人必承受土地,

在地上永远安居。

30义人口出智慧,诉说正义,

31铭记上帝的律法,

从不失脚。

32恶人窥探义人,

伺机谋害。

33但耶和华不会让恶人得逞,

也不会让义人在审判时被定罪。

34要等候耶和华,

坚守祂的道,

祂必赐你土地,使你有尊荣。

你必亲眼看见恶人被铲除。

35我见过邪恶残暴之人,

乍看如葱茏的黎巴嫩香柏树,

36再一看,

他已经消失得无影无踪,

无处可寻。

37你看那纯全正直、爱好和平的人,

他们前途美好。

38罪人必遭毁灭,

恶人必被铲除。

39耶和华拯救义人,

患难时作他们的庇护所。

40耶和华帮助他们,

拯救他们脱离恶人,

因为他们投靠祂。

New Amharic Standard Version

መዝሙር 37:1-40

መዝሙር 3737 የዚህ መዝሙር እያንዳንዱ ጥቅስ ተከታታይ ፊደላት ባሉት የዕብራይስጥ ሆህያት የሚጀምር ሲሆን፣ ጅማሬው ወይም ጅማሬውና መጨረሻው ትርጕም የሚሰጥ ግጥም ነው።

የጻድቁና የክፉው ዕጣ ፈንታ

የዳዊት መዝሙር።

1ዐመፀኞችን በማየት አትሸበር፤

በክፉ አድራጊዎችም አትቅና፤

2እንደ ሣር ፈጥነው ይደርቃሉና፤

እንደ ለምለም ቅጠልም ይጠወልጋሉ።

3በእግዚአብሔር ታመን፤ መልካምንም አድርግ፤

በምድሪቱ ተቀመጥ፤ ዘና ብለህ ተሰማራ።

4በእግዚአብሔር ደስ ይበልህ፤

የልብህንም መሻት ይሰጥሃል።

5መንገድህን ለእግዚአብሔር ዐደራ ስጥ፤

በእርሱ ታመን፤ እርሱም ያከናውንልሃል፤

6ጽድቅህን እንደ ብርሃን፣

ያንተን ፍትሕ እንደ ቀትር ፀሓይ ያበራዋል።

7በእግዚአብሔር ፊት ጸጥ በል፤

በትዕግሥትም ተጠባበቀው፤

መንገዱ በተቃናለት፣

ክፋትንም በሚሸርብ ሰው ልብህ አይሸበር።

8ከንዴት ተቈጠብ፤ ቍጣንም ተወው፤

ወደ እኵይ ተግባር እንዳይመራህ አትከፋ።

9ክፉ ሰዎች ይጠፋሉና፤

እግዚአብሔርን ተስፋ የሚያደርጉ ግን ምድርን ይወርሳሉ።

10ለአፍታ እንጂ፣ ክፉ ሰው አይዘልቅም፤

ስፍራውንም ብታሥሥ አታገኘውም።

11ገሮች ግን ምድርን ይወርሳሉ፤

በታላቅ ሰላምም ሐሤት ያደርጋሉ።

12ክፉዎች በጻድቃን ላይ ያሤራሉ፤

ጥርሳቸውንም ያፋጩባቸዋል።

13እግዚአብሔር ግን ይሥቅባቸዋል፣

ቀናቸው እንደ ደረሰ ያውቃልና።

14ድኾችንና ችግረኞችን ለመጣል፣

አካሄዳቸው ቀና የሆነውንም ለመግደል፣

ክፉዎች ሰይፋቸውን መዘዙ፤

ቀስታቸውንም ገተሩ።

15ሰይፋቸው የገዛ ልባቸውን ይወጋል፤

ቀስታቸውም ይሰበራል።

16የጻድቅ ጥቂት ሀብት፣

ከክፉዎች ብዙ ጥሪት ይበልጣል።

17የክፉዎች ክንድ ይሰበራልና፣

ጻድቃንን ግን እግዚአብሔር ደግፎ ይይዛቸዋል።

18እግዚአብሔር የንጹሓንን የሕይወት ዘመን ያውቃል፤

ርስታቸውም ለዘላለም ይኖራል።

19በክፉ ጊዜ ዐንገት አይደፉም፤

በራብ ዘመንም ይጠግባሉ።

20ክፉዎች ግን ይጠፋሉ፤

የእግዚአብሔር ጠላቶች እንደ መስክ ውበት ይሆናሉ፤

ይጠፋሉ፤ እንደ ጢስም ተነው ይጠፋሉ።

21ኀጢአተኛ ይበደራል፤ መልሶም አይከፍልም፤

ጻድቅ ግን ይቸራል።

22እግዚአብሔር የባረካቸው ምድርን ይወርሳሉ፤

እርሱ የሚረግማቸው ግን ይጠፋሉ።

23የሰው አካሄድ በእግዚአብሔር ይጸናል፤

በመንገዱ ደስ ይለዋል።

24ቢሰናከልም አይወድቅም፣

እግዚአብሔር በእጁ ደግፎ ይይዘዋልና።

25ጕልማሳ ነበርሁ፤ አሁን አርጅቻለሁ፤

ነገር ግን ጻድቅ ሲጣል፣

ዘሩም እንጀራ ሲለምን አላየሁም።

26ሁልጊዜ ቸር ነው፤ ያበድራልም፤

ልጆቹም የተባረኩ ይሆናሉ።

27ከክፉ ራቅ፤ መልካሙንም አድርግ፣

ለዘላለምም ትኖራለህ።

28እግዚአብሔር ፍትሕን ይወድዳልና፣

ታማኞቹንም አይጥልም፤

ለዘላለምም ይጠብቃቸዋል፤

የኀጢአተኛው ዘር ግን ይጠፋል።

29ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ፤

በእርሷም ለዘላለም ይኖራሉ።

30የጻድቅ አፍ ጥበብን ይናገራል፤

አንደበቱም ፍትሐዊ ነገር ያወራል።

31የአምላኩ ሕግ በልቡ አለ፤

አካሄዱም አይወላገድም።

32ክፉዎች ጻድቁን ይከታተሉታል፤

ሊገድሉትም ይሻሉ።

33እግዚአብሔር ግን በእጃቸው አይጥለውም፤

ፍርድ ፊት ሲቀርብም አሳልፎ አይሰጠውም።

34እግዚአብሔርን ደጅ ጥና፤

መንገዱንም ጠብቅ፤

ምድሪቱን ትወርስ ዘንድ ከፍ ከፍ ያደርግሃል፤

ክፉዎችም ሲጠፉ ታያለህ።

35ክፉና ጨካኙን ሰው፣

እንደ ሊባኖስ ዝግባ ለምልሞ አየሁት፤

36ዳግመኛ በዚያ ሳልፍ፣ እነሆ፣ በቦታው አልነበረም፤

ብፈልገውም አልተገኘም።

37ንጹሓንን ልብ በል፤ ቅኑንም አስተውል፤

የሰላም ሰው ተስፋ አለውና።37፥37 ወይም ዘር ይወጣለታል

38ኀጢአተኞች ግን በአንድነት ይጠፋሉ፤

የክፉዎችም ዘር37፥38 ወይም ትውልድ ይወገዳል።

39የጻድቃን ድነት ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው፤

በመከራ ጊዜም መጠጊያቸው እርሱ ነው።

40እግዚአብሔር ይረዳቸዋል፤

ይታደጋቸዋልም፤

ከክፉዎች እጅ ነጥቆ ያወጣቸዋል፤

እርሱን መጠጊያ አድርገዋልና ያድናቸዋል።