诗篇 18 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

诗篇 18:1-50

第 18 篇

大卫的胜利之歌

耶和华的仆人大卫的诗,交给乐长。当时耶和华从众仇敌和扫罗手中拯救了他,他向耶和华吟唱此诗。

1耶和华啊,你是我的力量,

我爱你。

2耶和华是我的磐石,我的堡垒,我的拯救者;

我的上帝是保护我的磐石,

我的盾牌,

是拯救我的力量,我的堡垒。

3我求告当受颂赞的耶和华,

祂救我脱离仇敌。

4死亡的锁链曾缠住我,

罪恶的狂流曾淹没我。

5阴间的绳索曾捆绑我,

死亡的陷阱曾威胁我。

6在苦难中我呼求耶和华,

向我的上帝求助。

祂从殿中垂听我的呼求,

我的声音达到祂耳中。

7祂一发怒,大地震动,

山的根基摇晃。

8祂的鼻孔冒烟,

口喷烈焰和火炭。

9祂拨开云天,脚踩密云,

亲自降临。

10祂乘着基路伯天使飞翔,

乘着风的翅膀疾驰。

11祂藏身于黑暗中,

四围以密云作幔幕。

12从祂面前的荣光中,

冰雹和火炭冲破云层。

13耶和华在天上打雷,

至高者发出的声音响彻在冰雹和火炭中。

14祂射出利箭驱散仇敌,

发出闪电击溃他们。

15耶和华啊,你斥责一声,

鼻孔一吹气,海底就显现,

大地也露出根基。

16祂从高天伸手抓住我,

从深渊中把我拉上来。

17祂救我脱离强敌,

脱离我无法战胜的仇敌。

18他们在我危难之时攻击我,

但耶和华扶持我。

19祂拯救我,领我到宽阔之地,

因为祂喜悦我。

20耶和华因我公义而善待我,

因我清白而赏赐我,

21因为我坚守祂的道,

没有作恶背弃我的上帝。

22我遵守祂的一切法令,

没有把祂的律例弃置一旁。

23我在祂面前纯全无过,

没有沾染罪恶。

24耶和华因我公义、

在祂面前清白而奖赏我。

25仁慈的人,你以仁慈待他;

纯全的人,你以纯全待他;

26纯洁的人,你以纯洁待他;

心术不正的人,你以计谋待他。

27你搭救谦卑的人,

贬抑眼目高傲的人。

28我的上帝耶和华啊,

你是我的明灯,

你使我的黑暗变为光明。

29我倚靠你的力量迎战敌军,

靠着我的上帝跃过墙垣。

30上帝的道完美,

耶和华的话纯全,

祂是投靠祂之人的盾牌。

31除了耶和华以外,谁是上帝呢?

除了我们的上帝,谁是磐石呢?

32是上帝赐我力量,

使我行为纯全。

33祂使我的脚如母鹿的蹄,

稳踏在高处。

34祂训练我,

使我的手能争战、

我的臂膀能拉开铜弓。

35耶和华啊,你是拯救我的盾牌,

你的右手扶持我,

你的垂顾使我强大。

36你使我脚下的道路宽阔,

不致滑倒。

37我追赶仇敌直到追上,

不消灭他们决不回头。

38我打垮他们,

使他们倒在我的脚下,

再也站不起来。

39你赐我征战的能力,

使我的仇敌降服在我脚下。

40你使我的仇敌狼狈而逃,

我歼灭了恨我的人。

41他们高声求救,却无人搭救;

他们呼求耶和华,祂也不应允。

42我把他们打得粉碎,

如同风中的灰尘;

我把他们倒掉,

如同街上的泥土。

43你救我脱离我百姓的攻击,

立我做列国的元首。

素不认识的民族也归顺我。

44他们望风而降,

外族人对我俯首称臣。

45外族人闻风丧胆,

战战兢兢地走出他们的城池。

46耶和华永远活着,

保护我的磐石当受颂赞,

拯救我的上帝当受尊崇。

47祂是为我申冤的上帝,

祂使列邦臣服于我。

48祂救我脱离仇敌,

使我胜过强敌,

拯救我脱离残暴之徒。

49因此,耶和华啊,

我要在列邦中赞美你,

歌颂你的名。

50你使你立的王大获全胜,

向你膏立的大卫及其后代广施慈爱,直到永远。

New Amharic Standard Version

መዝሙር 18:1-50

መዝሙር 18

የድል መዝሙር

18 ርእስ-50 ተጓ ምብ – 2ሳሙ 22፥1-51

ለመዘምራን አለቃ፤ የእግዚአብሔር ባሪያ የዳዊት መዝሙር፤ ይህም እግዚአብሔር ከሳዖልና ከጠላቶቹ ሁሉ እጅ በታደገው ጊዜ፣ ለእግዚአብሔር እንዲህ ሲል የዘመረው ነው፤

1ጕልበቴ እግዚአብሔር ሆይ፤ እወድድሃለሁ።

2እግዚአብሔር ዐለቴ፣ መጠጊያዬና ታዳጊዬ ነው፤

አምላኬ የምሸሸግበት ዐለቴ፤

እርሱ ጋሻዬ፣ የድነቴ ቀንድና18፥2 ቀንድ በዚህ ቦታ ብርታትን ያመለክታል። ዐምባዬ ነው።

3ምስጋና የሚገባውን እግዚአብሔርን እጠራለሁ፤

ከጠላቶቼም እድናለሁ።

4የሞት ገመድ ዐነቀኝ፤

የጥፋት ጐርፍም አጥለቀለቀኝ።

5የሲኦል18፥5 ወይም የመቃብር ገመድ ተጠመጠመብኝ፤

የሞት ወጥመድም ተጋረጠብኝ።

6በተጨነቅሁ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፤

እንዲረዳኝም ወደ አምላኬ ጮኽሁ፤

እርሱም ከመቅደሱ ድምፄን ሰማ፤

ጩኸቴም ከፊቱ ደረሰ፤ ወደ ጆሮውም ገባ።

7ምድር ተንቀጠቀጠች፤ ተናወጠችም፤

የተራሮችም መሠረት ተናጋ፤

ጌታ ተቈጥቷልና ተንቀጠቀጡ።

8ከአፍንጫው ጢስ ወጣ፤

የሚባላ እሳት ከአፉ፤

የፍም ነበልባል ከእርሱ ፈለቀ።

9ሰማያትን ሰንጥቆ ወረደ፤

ከእግሩም በታች ጥቍር ደመና ነበረ።

10በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ በረረ፤

በነፋስም ክንፍ መጠቀ።

11ጨለማን መሰወሪያው፣ በዙሪያውም አጐበሩ አደረገው፤

በዝናብ ዐዘል ጥቍር ደመናም ተሸፈነ።

12በፊቱ ካለው ብርሃን የተነሣ፣

ደመናት፣ የበረዶ ድንጋይና መብረቅ ወጡ።

13እግዚአብሔር ከሰማያት አንጐደጐደ፤

ልዑልም ድምፁን አስተጋባ።18፥13 አንዳንድ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆችና ሰብዓ ሊቃናት (በተጨማሪ 2ሳሙ 22፥14 ይመ) እንዲሁ ሲሆኑ፣ አብዛኛዎቹ የዕብራይስጥ የጥንት ቅጆች ግን …አስተጋባ፤ በድንጋይ ዝናብ በድንገተኛ መብረቅ መካከል የሚለውን ይጨምራሉ።

14ፍላጻውን አስፈንጥሮ በተናቸው፤

መብረቅ አዥጐድጕዶ አሳደዳቸው።

15እግዚአብሔር ሆይ፤ ከተግሣጽህ የተነሣ፣

ከአፍንጫህም እስትንፋስ የተነሣ፣

የባሕር ወለል ተገለጠ፤

የዓለምም መሠረት ዕራቍቱን ቀረ።

16ከላይ እጁን ወደ ታች ዘርግቶ ያዘኝ፤

ከብዙ ጥልቅ ውሃም አወጣኝ፤

17ከኀያላን ጠላቶቼ አዳነኝ፤

ከእኔ ከሚበረቱ ባላንጣዎቼም ታደገኝ።

18እነርሱ በመከራዬ ቀን መጡብኝ፤

እግዚአብሔር ግን ድጋፍ ሆነኝ።

19ወደ ሰፊ ስፍራ አወጣኝ፤

ደስ ተሰኝቶብኛልና አዳነኝ።

20እግዚአብሔር እንደ ጽድቄ መልሶልኛል፤

እንደ እጄ ንጽሕናም ከፍሎኛል፤

21የእግዚአብሔርን መንገድ ጠብቄአለሁና፤

አምላኬንም በመተው ክፉ አላደረግሁም።

22ሕጎቹ ሁሉ በፊቴ ናቸው፤

ሥርዐቱን ከፊቴ አላራቅሁም።

23በፊቱ ነቀፋ አልነበረብኝም፤

ራሴንም ከኀጢአት ጠብቄአለሁ።

24እግዚአብሔር እንደ ጽድቄ መጠን፣

በፊቱ እንደ እጄም ንጽሕና ከፍሎኛል።

25ከታማኙ ጋር ታማኝ ትሆናለህ፤

እንከን ከሌለበት ጋር ያለ እንከን ትሆናለህ፤

26ከንጹሑ ጋር ንጹሕ ሆነህ ትገኛለህ፤

ለጠማማው አንተ ትጠምበታለህ።

27አንተ ትሑታንን ታድናለህ፤

ትዕቢተኛውን ዐይን ግን ታዋርዳለህ።

28እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ መብራቴን ታበራለህ፤

አምላኬ ሆይ፤ ጨለማዬን ብርሃን ታደርገዋለህ።

29በአንተ ጕልበት በሰራዊት ላይ እረማመዳለሁ፤18፥29 ወይም …በመሰናክል ውስጥ መሮጥ እችላለሁ

በአምላኬም ኀይል ቅጥር እዘላለሁ።

30የአምላክ መንገድ ፍጹም ነው፤

የእግዚአብሔር ቃል የነጠረ ነው።

መጠጊያ ለሚያደርጉት ሁሉ፣

እርሱ ጋሻ ነው።

31ከእግዚአብሔር በቀር ማን አምላክ አለ?

ከአምላካችንስ በቀር ዐምባ ማን ነው?

32ኀይልን የሚያስታጥቀኝ፣

መንገዴንም የሚያቃና እግዚአብሔር ነው።

33እርሱ እግሮቼን እንደ ብሖር እግሮች ያደርጋል፤

በከፍታዎችም ላይ ያቆመኛል።

34እጆቼን ለጦርነት ያሠለጥናቸዋል፤

ክንዴም የናስ ቀስት መገተር ይችላል።

35የድል ጋሻ ሰጥተኸኛል፤

ቀኝ እጅህም ደግፋ ይዛኛለች፤

ዝቅ ብለህም ከፍ አደረግኸኝ።

36ከሥሬ ያለውን ስፍራ ለአረማመዴ አሰፋህልኝ፤

እግሬም አልተንሸራተተም።

37ጠላቶቼን አሳድጄ ያዝኋቸው፤

እስኪጠፉም ወደ ኋላዬ አልተመለስሁም።

38እንዳያንሰራሩ አድርጌ አደቀቅኋቸው፤

ከእግሬም ሥር ወደቁ።

39አንተ ለጦርነት ኀይልን አስታጠቅኸኝ፤

ባላንጦቼ እግሬ ላይ እንዲደፉ አደረግህ።

40ጠላቶቼ ወደ ኋላቸው እንዲሸሹ አደረግህ፤

እኔም የሚጠሉኝን አጠፋኋቸው።

41ለርዳታ ጮኹ፤ የሚያስጥላቸው ግን አላገኙም፤

ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፤ እርሱም አልመለሰላቸውም።

42ነፋስ ጠርጎ እንደሚወስደው ትቢያ አደቀቅኋቸው፤

እንደ መንገድ ላይ ጭቃም አውጥቼ ጣልኋቸው።

43ከሕዝብ ግርግር አወጣኸኝ፤

የሕዝቦች መሪ አድርገህ አስቀመጥኸኝ፤

የማላውቀውም ሕዝብ ተገዛልኝ።

44ትእዛዜን እንደ ሰሙ ይታዘዙልኛል፤

ባዕዳንም በፊቴ ዐንገት ደፉ።

45ባዕዳን በፍርሀት ተዋጡ፤

ከምሽጋቸውም እየተንቀጠቀጡ ወጡ።

46እግዚአብሔር ሕያው ነው! ዐምባዬ ይባረክ፤

ያዳነኝ አምላክ ከፍ ከፍ ይበል።

47እርሱ በቀሌን የሚመልስልኝ፣

ሕዝቦችንም የሚያስገዛልኝ አምላክ ነው፤

48ከጠላቶቼም የሚታደገኝ እርሱ ነው።

አንተ ከባላንጦቼ በላይ ከፍ ከፍ አደረግኸኝ፤

ከጨካኞች አዳንኸኝ።

49እግዚአብሔር ሆይ፤ ስለዚህ በአሕዛብ መካከል አመሰግንሃለሁ፤

ስምህንም በመዝሙር እወድሳለሁ።

50እርሱ ላነገሠው ታላላቅ ድሎችን ይሰጣል፤

ጽኑ ፍቅሩንም ለቀባው፣

ለዳዊትና ለዘሩ ለዘላለም ይገልጣል።