历代志下 30 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

历代志下 30:1-27

预备守逾越节

1希西迦派人通告以色列犹大全境,又写信通知以法莲人和玛拿西人,叫他们到耶路撒冷耶和华的殿,向以色列的上帝耶和华守逾越节。 2王、众官员及耶路撒冷的全体会众决定在二月守逾越节。 3他们不能在一月守节期,因为洁净自己的祭司不够多,民众也没有聚集在耶路撒冷4王与全体会众都很赞成这个计划。 5于是,他们下令通告全以色列,从别示巴直到,让人们到耶路撒冷以色列的上帝耶和华守逾越节,因为人们不常照律例守这节期。

6信差遵照王的命令带着王和众官员的信走遍以色列犹大,宣告说:“以色列人啊,你们应当归向亚伯拉罕以撒以色列的上帝耶和华,好使祂转向你们这些从亚述王手中逃脱的余民。 7不要效法你们的祖先和亲族,他们对他们祖先的上帝耶和华不忠,以致耶和华使他们的下场很可怕,正如你们所见的。 8现在,不要像你们的祖先那样顽固不化;要顺服耶和华,进入祂永远圣洁的圣所,事奉你们的上帝耶和华,好使祂的烈怒转离你们。 9你们若归向祂,你们的弟兄和儿女必蒙掳走他们之人的怜悯,得以回归此地,因为你们的上帝耶和华有恩典,好怜悯。你们若归向祂,祂必不会转脸不顾你们。”

10信差将这通告逐城传遍以法莲玛拿西,直到西布伦,可是那些地方的人却嘲笑、戏弄他们。 11然而,有些亚设人、玛拿西人和西布伦人谦卑悔改,来到耶路撒冷12耶和华上帝感动犹大人,使他们一心遵从王与众官员奉祂的指示所下的命令。

守逾越节

13二月,大群的人聚到耶路撒冷守除酵节。 14他们除去耶路撒冷的祭坛和所有香坛,把它们丢进汲沦溪。 15二月十四日,他们宰了逾越节的羊羔。祭司和利未人觉得惭愧,就洁净自己,把燔祭带到耶和华的殿里, 16然后照上帝的仆人摩西的律法照常供职。祭司从利未人手中接过血,洒在坛上。 17因为会众中间有许多人没有洁净自己,利未人就为所有不洁之人宰逾越节的羊羔献给耶和华。 18-19有许多以法莲人、玛拿西人、以萨迦人和西布伦人没有洁净自己就吃了逾越节的羊羔,违背了律法的规定。希西迦就为他们祷告说:“凡诚心寻求他祖先的上帝耶和华的人,虽然没有照圣所的律例洁净自己,愿良善的耶和华赦免他!” 20耶和华垂听希西迦的祷告,就赦免30:20 赦免”希伯来文是“医治”。了他们。

21耶路撒冷以色列人非常喜乐地守除酵节七天。利未人和祭司用响亮的乐器天天颂赞耶和华。 22希西迦慰劳所有善于事奉耶和华的利未人。于是,众人欢宴过节七天,又献上平安祭,称谢他们祖先的上帝耶和华。

再次守节期

23全体会众商议要再守节期七天,于是大家又欢欢喜喜地守节期七天。 24犹大希西迦送给会众一千头公牛和七千只羊,众官员也送给会众一千头公牛和一万只羊,并且很多祭司都已洁净自己。 25犹大全体会众、祭司、利未人和从以色列来的全体会众,以及寄居在以色列犹大的人尽都欢喜。 26耶路撒冷都喜气洋洋,因为自以色列大卫的儿子所罗门时代以来,耶路撒冷从未有过这样的盛会。 27利未祭司起来为民众祝福,他们的祷告得蒙垂听,达到天上的圣所。

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 30:1-27

ሕዝቅያስ ፋሲካን ማክበሩ

1ሕዝቅያስ የእስራኤልን አምላክ የእግዚአብሔርን ፋሲካ ለማክበር በኢየሩሳሌም ወዳለው ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንዲመጡ፣ ለመላው እስራኤልና ለይሁዳ መልእክት ላከ፤ ለኤፍሬምና ለምናሴም ደብዳቤ ጻፈ። 2ንጉሡ፣ ሹማምቱና መላው የኢየሩሳሌም ጉባኤ የፋሲካውን በዓል በሁለተኛው ወር ለማክበር ተስማሙ። 3በቂ ካህናት ራሳቸውን ስላልቀደሱና ሕዝቡም ገና በኢየሩሳሌም ስላልተሰበሰቡ፣ በዓሉን በወቅቱ ለማክበር አልቻሉም ነበር። 4ንጉሡና መላው ጉባኤም ዕቅዱ ትክክል ሆኖ አገኙት። 5ስለዚህ የእስራኤልን አምላክ የእግዚአብሔርን ፋሲካ ለማክበር ሕዝቡ እንዲመጣ፣ ከቤርሳቤህ እስከ ዳን ድረስ ዐዋጅ እንዲነገር ወሰኑ፤ በተጻፈው መሠረት በዓሉ ብዛት ባለው ሕዝብ ተከብሮ አያውቅም ነበርና።

6መልእክተኞችም በንጉሡ ትእዛዝ፣ የንጉሡንና የሹማምቱን ደብዳቤ ይዘው ወደ እስራኤልና ወደ ይሁዳ ሁሉ ሄዱ፤ ደብዳቤውም እንዲህ የሚል ነበር፤

“የእስራኤል ሕዝብ ሆይ፤ እርሱ ወደ ተረፋችሁት፣ ከአሦር ነገሥታትም እጅ ወዳመለጣችሁት፣ ወደ እናንተ እንዲመለስ እናንተም የአብርሃም፣ የይስሐቅና የእስራኤል አምላክ ወደ ሆነው ወደ እግዚአብሔር ተመለሱ። 7እንደምታዩት ሁሉ መሣለቂያ እስኪያደርጋቸው ድረስ፣ ለአባቶቻቸው አምላክ ለእግዚአብሔር እንዳልታመኑ እንደ አባቶቻችሁና እንደ ወንድሞቻችሁ አትሁኑ። 8እንደ አባቶቻችሁም ዐንገተ ደንዳኖች አትሁኑ፤ ለእግዚአብሔር ተገዙ፤ እርሱ ለዘላለም ወደ ቀደሰውም መቅደስ ኑ። አስፈሪ ቍጣው ከእናንተ እንዲመለስም፣ እግዚአብሔር አምላካችሁን አገልግሉ። 9እናንተ ወደ እግዚአብሔር ብትመለሱ፣ አምላካችሁ እግዚአብሔር ቸርና ርኅሩኅ ስለሆነ ወንድሞቻችሁና ልጆቻችሁን በማረኳቸው ዘንድ ምሕረትን ያገኛሉ፤ ወደዚህች ምድር ይመለሳሉ። እናንተ ወደ እርሱ ብትመለሱ፣ እርሱም ፊቱን ከእናንተ አይመልስም።”

10መልእክተኞቹም በኤፍሬምና በምናሴ ምድር ከአንዱ ከተማ ወደ ሌላው ከተማ በመዘዋወር እስከ ዛብሎን ድረስ ሄዱ፤ ሕዝቡ ግን አንቋሸሻቸው፤ ተሣለቀባቸውም። 11ሆኖም ከአሴር፣ ከምናሴና ከዛብሎን ጥቂት ሰዎች ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ወደ ኢየሩሳሌም መጡ። 12እንዲሁም ንጉሡና ሹማምቱ በእግዚአብሔር ቃል መሠረት ያዘዙትን እንዲፈጽሙ አንድ ልብ ይሰጣቸው ዘንድ የእግዚአብሔር እጅ በይሁዳ ላይ ነበር።

13በሁለተኛው ወር የቂጣን በዓል ለማክበር እጅግ ብዙ ሕዝብ በኢየሩሳሌም ተሰበሰበ። 14በኢየሩሳሌም የነበሩትን መሠዊያዎች ነቃቅለው፣ የዕጣን መሠዊያዎችንም ከስፍራው አንሥተው ወደ ቄድሮን ሸለቆ ጣሉ።

15በሁለተኛው ወር በዐሥራ አራተኛው ቀን የፋሲካውን በግ ዐረዱ። ካህናቱና ሌዋውያኑ ዐፍረው ስለ ነበር ራሳቸውን ቀደሱ፤ የሚቃጠል መሥዋዕትንም ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አመጡ። 16ከዚያም በእግዚአብሔር ሰው በሙሴ ሕግ እንደ ታዘዘው መደበኛ ቦታቸውን ያዙ። ካህናቱም ከሌዋውያኑ እጅ የተቀበሉትን ደም ረጩ። 17ከጉባኤው መካከል አብዛኛዎቹ ራሳቸውን ያልቀደሱ ስለ ነበሩ፣ ሌዋውያኑ በሥርዐቱ መሠረት ራሳቸውን ላላነጹትና ጠቦቶቻቸውን ለእግዚአብሔር መቀደስ ላልቻሉት ሁሉ የፋሲካውን በጎች ማረድ ነበረባቸው። 18ምንም እንኳ ከኤፍሬም፣ ከምናሴ፣ ከይሳኮርና ከዛብሎን ከመጡት አብዛኛዎቹ ራሳቸውን ያላነጹ ቢሆንም ከተጻፈው ትእዛዝ ውጭ ፋሲካውን በሉ። ሕዝቅያስ ግን እንዲህ ሲል ጸለየ፤ “ቸሩ እግዚአብሔር ሆይ፤ ይቅር በላቸው፤ 19ምንም እንኳ በመቅደሱ ሥርዐት መሠረት የነጹ ሆነው ባይገኙም፣ የአባቶቻቸው አምላክ የሆነውን እግዚአብሔር አምላካቸውን ለመፈለግ ልባቸውን የሚያዘጋጁትን ሁሉ ይቅር በላቸው።” 20እግዚአብሔርም ሕዝቅያስን ሰማው፤ ሕዝቡንም ፈወሰ።

21ሌዋውያኑና ካህናቱ በእግዚአብሔር የዜማ ዕቃ ታጅበው፣ በየዕለቱ ለእግዚአብሔር እየዘመሩ30፥21 ወይም ሌዋውያንና ካህናቱ በእግዚአብሔር የዜማ ዕቃ ታጅበው በየዕለቱ እግዚአብሔርን ያመሰግኑ ነበር።፣ በኢየሩሳሌም የነበሩት እስራኤላውያን የቂጣን በዓል በታላቅ ደስታ ለሰባት ቀን አከበሩ፤

22ሕዝቅያስም በእግዚአብሔር አገልግሎት አስተዋዮች የነበሩትን ሌዋውያን ሁሉ በንግግሩ አበረታታ። ሰባቱንም ቀን የተወሰነላቸውን ድርሻ እየበሉና የኅብረት መሥዋዕቱንም30፥22 በትውፊት፣ የሰላም መሥዋዕት ይባላል። እያቀረቡ የአባቶቻቸውን አምላክ እግዚአብሔርን አመሰገኑ።

23ጉባኤውም ሁሉ በተከታዩ ሰባት ቀን በዓሉን እንደ ገና ለማክበር ተስማሙ፣ ስለዚህ በዓሉን ለሰባት ተጨማሪ ቀን በታላቅ ደስታ አከበሩ። 24የይሁዳ ንጉሥ ሕዝቅያስ አንድ ሺሕ ወይፈን፣ ሰባት ሺሕ በግና ፍየል ለጉባኤው ሰጠ፤ ሹማምቱም እንደዚሁ አንድ ሺሕ ወይፈን፣ ዐሥር ሺሕ በግና ፍየል ሰጡ። እጅግ ብዙ ካህናትም ራሳቸውን ቀደሱ። 25መላው የይሁዳ ጉባኤ፣ ካህናቱና ሌዋውያኑ፣ ከእስራኤል የተሰበሰበው ጉባኤ ሁሉ፣ እንዲሁም ከእስራኤል የመጡ መጻተኞችና በይሁዳ የሚኖሩ መጻተኞች ደስ አላቸው። 26ከእስራኤል ንጉሥ ከዳዊት ልጅ ከሰሎሞን ጊዜ አንሥቶ በኢየሩሳሌም እንዲህ ያለ በዓል ተደርጎ ስለማያውቅ፣ በኢየሩሳሌም ታላቅ ደስታ ሆነ። 27ከዚያም ካህናቱና ሌዋውያኑ ተነሥተው ሕዝቡን ባረኩ፤ እግዚአብሔርም ሰማቸው፤ ጸሎታቸውም ወደ ሰማይ ወደ ቅዱሱ ማደሪያው ደረሰ።