利未记 17 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

利未记 17:1-16

杀祭牲的条例

1耶和华对摩西说: 2“你把以下条例告诉亚伦父子们及全体以色列人。

3“任何在营内或营外宰杀公牛、绵羊或山羊的以色列人, 4若没有把牲畜带到会幕门口,在耶和华的圣幕前献给耶和华,便是犯了流血之罪,要将他从民中铲除。 5这是为促使以色列人把祭牲带到会幕门口交给祭司,献给耶和华作平安祭,而非在野外杀祭牲献祭。 6祭司要将祭牲的血洒在会幕门口耶和华的祭坛上,把脂肪焚烧献给耶和华作馨香之祭。 7他们不可再献祭物给山羊神,与其苟合。这是一条永远不变的律例,他们世世代代都要遵守。 8不论是以色列人,还是寄居在以色列人中间的外族人,献燔祭或其他祭物时, 9如果有人没把祭物带到会幕门口献给耶和华,要将他从民中铲除。

禁止吃血

10“任何以色列人或寄居在以色列人中间的外族人若吃血,耶和华必严惩,把他从民中铲除。 11因为生命在血中,耶和华把血赐给你们,使你们可以用血在祭坛上为自己赎罪。血可以为人的生命赎罪。 12所以耶和华吩咐以色列人和寄居在以色列人中间的外族人不可吃血。 13以色列人或寄居在以色列人中间的外族人如果捕到可吃的鸟或兽,必须放尽它的血,用土掩埋, 14因为众生的生命都在血中。因此,耶和华吩咐以色列人不可吃任何动物的血,因为血就是生命。凡吃血的都要被铲除。 15不论以色列人还是外族人,若吃了自然死亡或被野兽撕裂的动物,就不洁净。他必须洗衣、沐浴,等到傍晚才能洁净, 16否则他要承担罪责。”

New Amharic Standard Version

ዘሌዋውያን 17:1-16

ደም መብላት ስለ መከልከሉ

1እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴን እንዲህ አለው፤ 2“ለአሮንና ለልጆቹ፣ ለእስራኤላውያንም ሁሉ እንዲህ ብለህ ንገራቸው፤ ‘እግዚአብሔር (ያህዌ) ያዘዘው ይህ ነው፤ 3ማንኛውም እስራኤላዊ በሰፈር ውስጥ ወይም ከሰፈር ውጭ በሬ፣17፥3 የዕብራይስጡ ቃል ተባዕትና እንስትን ሊያጠቃልል ይችላል። በግ ወይም ፍየል ቢያርድ፣ 4በእግዚአብሔር (ያህዌ) ማደሪያ ፊት ለእግዚአብሔር (ያህዌ) መሥዋዕት አድርጎ ለማቅረብ ወደ መገናኛው ድንኳን ደጃፍ ባያመጣው፣ ያ ሰው በከንቱ ደም እንዳፈሰሰ ይቈጠራል፤ ደም በማፍሰሱም ከወገኖቹ ተለይቶ ይጥፋ። 5እስራኤላውያን የሚሠዉትን መሥዋዕት ወደ እግዚአብሔር (ያህዌ) የሚያመጡበት ምክንያት ይህ ነው። ይህንም ካህኑ ዘንድ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ አምጥተው ለእግዚአብሔር (ያህዌ) የኅብረት መሥዋዕት17፥5 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል በማድረግ ያቅርቡ። 6ካህኑም ደሙን በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ባለው በእግዚአብሔር (ያህዌ) መሠዊያ ላይ ይርጭ፤ ሥቡንም እግዚአብሔርን (ያህዌ) ደስ የሚያሰኝ ሽታ እንዲሆን ያቃጥል። 7ከዚህ በፊት ላመነዘሩባቸው አጋንንት17፥7 ወይም የፍየል ጣዖታት ከእንግዲህ ወዲህ ማንኛውንም መሥዋዕት ሊሠዉ አይገባም። ይህ ለእነርሱና ከእነርሱ በኋላ ለሚነሣው ትውልድ ሁሉ የዘላለም ሥርዐት ይሁን።’

8“እንዲህም በላቸው፤ ‘የሚቃጠል መሥዋዕት ወይም ሌላ መሥዋዕት የሚያቀርብ ማንኛውም እስራኤላዊ ወይም በመካከላቸው የሚኖር ማንኛውም መጻተኛ፣ 9ወደ መገናኛው ድንኳን ደጃፍ ለእግዚአብሔር (ያህዌ) ባያቀርብ፣ ያ ሰው ከወገኖቹ ተለይቶ ይጥፋ።

10“ ‘ማንኛውም እስራኤላዊ ወይም በመካከላቸው የሚኖር ማንኛውም መጻተኛ ደም ቢበላ፣ ደም በሚበላው በዚያ ሰው ላይ ፊቴን አከብድበታለሁ፤ ከወገኖቹም ለይቼ አጠፋዋለሁ፤ 11የፍጡር ሕይወት በደሙ ውስጥ ነውና፤ በመሠዊያ ላይ ለሕይወታችሁ ማስተስረያ እንዲሆን ደሙን ሰጥቻችኋለሁ፤ ለሰውም ሕይወት ስርየት የሚያስገኝ ደም ነው። 12ስለዚህ እስራኤላውያንን፣ “ከእናንተ ማንም ደም አይብላ፤ በመካከላችሁ የሚኖር መጻተኛም ቢሆን ደም አይብላ” አልሁ።

13“ ‘እንዲበላ የተፈቀደውን ማንኛውንም እንስሳ ወይም ወፍ ዐድኖ የያዘ ማንኛውም እስራኤላዊ ወይም በመካከላችሁ የሚኖር ማንኛውም መጻተኛ ደሙን ከውስጡ ያፍስስ፤ ዐፈርም ያልብሰው፤ 14የማንኛውም ፍጡር ሕይወት ደሙ ነውና። ስለዚህ እስራኤላውያንን፣ “የፍጡር ሁሉ ሕይወት ደሙ ነውና የማንኛውንም ፍጡር ደም አትብሉ፤ የበላው ሰው ሁሉ ተለይቶ ይጥፋ” አልኋቸው።

15“ ‘ሞቶ የተገኘውን ወይም አውሬ የዘነጠለውን የበላ ማንኛውም የአገር ተወላጅ ወይም መጻተኛ ልብሱን ይጠብ፤ ሰውነቱንም በውሃ ይታጠብ፤ በሥርዐቱ መሠረት እስከ ማታ ድረስ ርኩስ ይሆናል፤ ከዚያም በኋላ ንጹሕ ይሆናል። 16ልብሱን ባያጥብ፣ ሰውነቱንም ባይታጠብ ግን ኀጢአት ሠርቷልና ይጠየቅበታል።’ ”