1เธสะโลนิกา 1 – TNCV & NASV

Thai New Contemporary Bible

1เธสะโลนิกา 1:1-10

1จดหมายฉบับนี้จากข้าพเจ้าเปาโล สิลาส1:1 ภาษากรีกว่าสิลวานัส และทิโมธี

ถึงคริสตจักรของชาวเธสะโลนิกาในพระเจ้าพระบิดาและองค์พระเยซูคริสต์เจ้า

ขอพระคุณและสันติสุขมีแก่ท่านทั้งหลาย1:1 สำเนาต้นฉบับเก่าแก่บางสำเนาว่าแก่ท่านทั้งหลายจากพระเจ้าพระบิดาของเราและองค์พระเยซูคริสต์เจ้า

ขอบพระคุณและทูลขอ

2เราขอบพระคุณพระเจ้าเนื่องด้วยพวกท่านทั้งปวงและอธิษฐานเผื่อท่านเสมอ 3ต่อหน้าพระเจ้าพระบิดาของเรา เราระลึกอยู่เสมอไม่ได้ขาดถึงการงานของท่านที่เกิดจากความเชื่อ ถึงการลงแรงทำงานหนักของท่านที่เป็นผลจากความรัก และถึงการสู้ทนของท่านที่รับแรงบันดาลใจจากความหวังในองค์พระเยซูคริสต์เจ้าของเรา

4พี่น้องทั้งหลายผู้เป็นที่รักของพระเจ้า เรารู้ว่าพระองค์ทรงเลือกสรรท่าน 5เพราะข่าวประเสริฐของเรามาถึงท่านไม่ใช่เพียงด้วยถ้อยคำเท่านั้น แต่ด้วยฤทธิ์อำนาจ ด้วยพระวิญญาณบริสุทธิ์และด้วยความเชื่อมั่นอันลึกซึ้ง ท่านทราบว่าเราใช้ชีวิตอย่างไรในหมู่พวกท่านเพื่อเห็นแก่ท่าน 6ท่านได้ทำตามอย่างเราและองค์พระผู้เป็นเจ้า ทั้งๆ ที่ต้องทนทุกข์อย่างหนักท่านก็รับข่าวประเสริฐด้วยความชื่นชมยินดีซึ่งพระวิญญาณบริสุทธิ์ประทาน 7ดังนั้นท่านจึงเป็นแบบอย่างแก่ผู้เชื่อทั้งปวงในแคว้นมาซิโดเนียและแคว้นอาคายา 8ข่าวประเสริฐขององค์พระผู้เป็นเจ้าเลื่องลือจากพวกท่านออกไป ไม่เฉพาะในแคว้นมาซิโดเนียและแคว้นอาคายา ความเชื่อในพระเจ้าของท่านยังโด่งดังไปทั่วทุกหนแห่ง ฉะนั้นเราจึงไม่ต้องพูดถึงอีก 9เพราะเขาเหล่านั้นเองเล่าขานว่าพวกท่านต้อนรับเราอย่างไร และยังบอกว่าท่านได้หันจากรูปเคารพมาหาพระเจ้าเพื่อรับใช้พระเจ้าเที่ยงแท้ผู้ทรงพระชนม์อยู่ 10และรอคอยพระบุตรของพระองค์จากสวรรค์ผู้ซึ่งพระองค์ทรงให้เป็นขึ้นจากตาย คือพระเยซูผู้ทรงช่วยเราทั้งหลายจากพระพิโรธที่จะมาถึง

New Amharic Standard Version

1 ተሰሎንቄ 1:1-10

1ከጳውሎስ፣ ከሲላስና1፥1 ግሪኩ ሲልዋኑስ ይላል። ከጢሞቴዎስ፤

በእግዚአብሔር አብና በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ለሆኑት ለተሰሎንቄ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን፤

ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን1፥1 አንዳንድ ቅጆች ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ የሚለው የላቸውም።

ስለ ተሰሎንቄ ሰዎች እምነት የቀረበ ምስጋና

2በጸሎታችን እያስታወስናችሁ ሁልጊዜ እግዚአብሔርን ስለ ሁላችሁ እናመሰግናለን። 3ከእምነት የሆነውን ሥራችሁን፣ ከፍቅር የመነጨውን ድካማችሁንና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ባላችሁ ተስፋ የተገኘውን ጽናታችሁን በአምላካችንና በአባታችን ፊት ዘወትር እናስባለን።

4በእግዚአብሔር የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ፤ እርሱ እንደ መረጣችሁ እናውቃለን፤ 5ምክንያቱም ወንጌላችን ወደ እናንተ የመጣው በኀይልና በመንፈስ ቅዱስ፣ በብዙም መረዳት እንጂ በቃል ብቻ አይደለም። ደግሞ ስለ እናንተ ስንል በመካከላችሁ እንዴት እንደ ኖርን ታውቃላችሁ። 6እናንተ እኛንና ጌታን መስላችኋል፤ ምንም እንኳ ብርቱ መከራ ቢደርስባችሁም፣ ቃሉን በመንፈስ ቅዱስ ደስታ ተቀብላችኋል። 7ከዚህም የተነሣ በመቄዶንያና በአካይያ ለሚገኙ ምእመናን መልካም ምሳሌ ሆናችኋል። 8የጌታ ቃል ከእናንተ ወጥቶ በመቄዶንያና በአካይያ መሰማቱ ብቻ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ያላችሁ እምነት በሁሉ ቦታ ታውቋል፤ ስለዚህ እኛ በዚህ ጕዳይ ላይ ምንም መናገር አያስፈልገንም፤ 9በእንዴት ያለ አቀባበል እንደ ተቀበላችሁንና ሕያውና እውነተኛ የሆነውን አምላክ ለማገልገል ከጣዖታት ወደ እግዚአብሔር እንዴት እንደ ተመለሳችሁ እነርሱ ራሳቸው ይናገራሉ፤ 10ደግሞም ከሙታን ያስነሣውንና ከሰማይ የሚመጣውን ልጁን፣ ከሚመጣውም ቍጣ የሚያድነንን ኢየሱስን እንዴት እንደምትጠባበቁ ይናገራሉ።