เศคาริยาห์ 13 – TNCV & NASV

Thai New Contemporary Bible

เศคาริยาห์ 13:1-9

ชำระบาป

1“ในวันนั้นจะมีน้ำพุพุ่งขึ้นมาสำหรับพงศ์พันธุ์ดาวิดและชาวเยรูซาเล็ม เพื่อชำระเขาทั้งปวงจากบาปและมลทินของเขา

2“ในวันนั้นเราจะทำลายรูปเคารพทั้งปวงให้สิ้นชื่อจากทั่วดินแดนนั้น จะไม่มีใครนึกถึงรูปเคารพเหล่านั้นอีก” พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ประกาศดังนั้น “เราจะกำจัดทั้งผู้พยากรณ์เท็จและวิญญาณโสโครกไปจากแผ่นดิน 3และหากผู้ใดยังขืนพยากรณ์ พ่อแม่ผู้ให้กำเนิดเขาเองจะกล่าวกับเขาว่า ‘เจ้าต้องตายเพราะเจ้าพูดเท็จในพระนามพระยาห์เวห์’ เมื่อเขาพยากรณ์ พ่อแม่ของเขาเองจะแทงเขา

4“ในวันนั้นผู้เผยพระวจนะทุกคนจะอับอายที่เห็นนิมิต จะไม่มีใครสวมเสื้อผ้าขนสัตว์แบบผู้เผยพระวจนะเพื่อตบตาประชาชนอีก 5เขาจะพูดว่า ‘ข้าพเจ้าไม่ใช่ผู้เผยพระวจนะ แต่เป็นชาวไร่ชาวนา อาศัยแผ่นดินเป็นที่ทำกินมาตั้งแต่หนุ่มๆ13:5 หรือชาวนา ชายคนหนึ่งขายข้าพเจ้ามาตั้งแต่หนุ่ม6หากมีใครถามเขาว่า ‘ก็แล้วรอยแผลเป็นพวกนี้บนตัวเจ้า13:6 หรือรอยแผลระหว่างมือทั้งสองของเจ้าหมายความว่าอะไร’ เขาจะตอบว่า ‘เป็นแผลที่ได้มาจากบ้านเพื่อน’ ”

คนเลี้ยงแกะถูกเล่นงาน ฝูงแกะกระจัดกระจาย

7พระยาห์เวห์ผู้ทรงฤทธิ์ประกาศว่า

“ดาบเอ๋ย จงตื่นขึ้น ห้ำหั่นคนเลี้ยงแกะของเรา

และคนใกล้ชิดของเรา

จงฟาดฟันคนเลี้ยงแกะ

และแกะจะกระจัดกระจายไป

และเราจะตวัดมือฟาดผู้เล็กน้อย”

8องค์พระผู้เป็นเจ้าประกาศว่า

“สองในสามของทั้งดินแดนจะถูกห้ำหั่นพินาศไป

เหลือไว้เพียงหนึ่งในสาม

9หนึ่งในสามนี้เราจะเอาไปใส่ในไฟ

เราจะถลุงพวกเขาเหมือนเงิน

และทดสอบพวกเขาเหมือนทองคำ

พวกเขาจะร้องเรียกนามของเรา

และเราจะตอบพวกเขา

เราจะกล่าวว่า ‘พวกเขาเป็นประชากรของเรา’

และพวกเขาจะกล่าวว่า ‘พระยาห์เวห์เป็นพระเจ้าของเรา’ ”

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 13:1-9

ከኀጢአት መንጻት

1“በዚያ ቀን የዳዊትን ቤትና የኢየሩሳሌምን ነዋሪዎች ከኀጢአትና ከርኩሰት የሚያነጻ ምንጭ ይከፈታል።

2“በዚያ ቀን የጣዖታትን ስም ከምድሪቱ አጠፋለሁ፤ ከእንግዲህም አይታሰቡም” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት። “ነቢያትንና ርኩስ መንፈስን ከምድሪቱ አስወግዳለሁ። 3ማንም ትንቢት ቢናገር ወላጅ አባትና እናቱ፣ ‘በእግዚአብሔር ስም ሐሰት ተናግረሃልና ሞት ይገባሃል’ ይሉታል። ትንቢት ሲናገርም የገዛ ወላጆቹ ይወጉታል።

4“በዚያን ቀን እያንዳንዱ ነቢይ ስለሚናገረው የትንቢት ራእይ ያፍራል፤ ለማታለልም የነቢያትን ጠጕራም ልብስ አይለብስም። 5እርሱም፣ ‘እኔ ገበሬ እንጂ ነቢይ አይደለሁም፤ ከልጅነቴ13፥5 ወይም ዐራሽ፤ በወጣትነቴ የተሸጥሁ ሰው ጀምሮ ኑሮዬ የተመሠረተውም በዕርሻ ላይ ነው’ ይላል። 6አንድ ሰው፣ ‘ይህ በሰውነትህ13፥6 በእጆችህ መኻል ያሉ ቍሰሎች የሚሉ አሉ። ላይ ያለው ቍስል ምንድን ነው?’ ብሎ ቢጠይቀው፣ ‘በባልንጀሮቼ ቤት ሳለሁ የቈሰልሁት ነው’ ይላል።”

እረኛው ተመታ፤ በጎቹ ተበተኑ

7እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤

“ሰይፍ ሆይ፤ በእረኛዬ፣

በቅርብ ወዳጄ ላይ ንቃ!

እረኛውን ምታ፣

በጎቹ ይበተናሉ፤

እኔም ክንዴን ወደ ታናናሾቹ አዞራለሁ።”

8እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “የምድር ሁሉ፣

ሁለት ሦስተኛው ተመትቶ ይጠፋል፤

አንድ ሦስተኛው ግን በውስጡ ይቀራል፤

9ይህን አንድ ሦስተኛውን ክፍል ወደ እሳት አመጣለሁ፤

እንደ ብር አነጥራቸዋለሁ፤

እንደ ወርቅም እፈትናቸዋለሁ፤

እነርሱ ስሜን ይጠራሉ፤

እኔም እመልስላቸዋለሁ፤

እኔም፣ ‘ሕዝቤ ናቸው’ እላለሁ፤

እነርሱም፣ ‘እግዚአብሔር አምላካችን ነው’ ይላሉ።”