پيدايش 16 – PCB & NASV

Persian Contemporary Bible

پيدايش 16:1‏-16

هاجر و اسماعيل

1‏-3اما سارای زن ابرام، بچه‌دار نمی‌شد؛ پس او كنيز مصری خود هاجر را به ابرام داد و گفت: «خداوند به من فرزندی نداده است، پس تو با اين كنيز همبستر شو تا برای من فرزندی به دنيا آوَرَد.» ابرام با پيشنهاد سارای موافقت نمود. (اين جريان ده سال پس از ورود ابرام به كنعان اتفاق افتاد.) 4ابرام با هاجر همبستر شد و او آبستن گرديد. هاجر وقتی دريافت كه حامله است، مغرور شد و از آن پس، بانويش سارای را تحقير می‌كرد.

5سارای به ابرام گفت: «تقصير توست كه اين كنيز مرا حقير می‌شمارد. خودم او را به تو دادم، ولی از آن لحظه‌ای كه فهميد آبستن است، مرا تحقير می‌كند. خداوند خودش حق مرا از تو بگيرد.»

6ابرام جواب داد: «او كنيز توست، هر طور كه صلاح می‌دانی با او رفتار كن.» پس سارای بنای بدرفتاری با هاجر را گذاشت و او از خانه فرار كرد.

7‏-8در بيابان، فرشتهٔ خداوند هاجر را نزديک چشمه‌ای كه سر راه «شور» است، يافت. فرشتهٔ خداوند پرسيد: «ای هاجر، كنيز سارای، از كجا آمده‌ای و به كجا می‌روی؟»

گفت: «من از خانهٔ بانويم گريخته‌ام.»

9‏-11فرشتهٔ خداوند فرمود: «نزد بانوی خود برگرد و مطيع او باش. من نسل تو را بی‌شمار می‌گردانم. اينک تو حامله هستی، و پسری خواهی زاييد. نام او را اسماعيل (يعنی ”خدا می‌شنود“) بگذار، چون خداوند آه و نالهٔ تو را شنيده است. 12پسر تو وحشی خواهد بود و با برادران خود سر سازگاری نخواهد داشت. او بر ضد همه و همه بر ضد او خواهند بود.»

13هاجر با خود گفت: «آيا براستی خدا را ديدم و زنده ماندم؟» پس خداوند را كه با او سخن گفته بود «اَنتَ ايل رُئی» (يعنی «تو خدايی هستی كه می‌بينی») ناميد. 14به همين جهت چاهی كه بين قادش و بارد است «بئرلَحَی رُئی» (يعنی «چاه خدای زنده‌ای كه مرا می‌بيند») ناميده شد.

15هاجر برای ابرام پسری زاييد و ابرام او را اسماعيل ناميد. 16در اين زمان ابرام هشتاد و شش ساله بود.

New Amharic Standard Version

ዘፍጥረት 16:1-16

አጋርና እስማኤል

1የአብራም ሚስት ሦራ፣ ልጆች አልወለደችለትም ነበር፤ እርሷም አጋር የምትባል ግብፃዊት አገልጋይ ነበረቻት። 2አብራምንም፣ “እግዚአብሔር (ያህዌ) ልጅ እንዳልወልድ አድርጎኛል። ምናልባት በእርሷ በኩል ልጆች አገኝ እንደሆን ሄደህ ከአገልጋዬ ጋር ተኛ” አለችው።

አብራምም ሦራ ባለችው ተስማማ። 3አብራም በከነዓን ምድር ዐሥር ዓመት ከኖረ በኋላ ሚስቱ ሦራ ግብፃዊት አገልጋይዋን አጋርን ሚስት እንድትሆነው ለባሏ ሰጠችው። 4አብራምም ከአጋር ጋር ተኛ፤ እርሷም ፀነሰች። አጋርም ነፍሰ ጡር መሆኗን ባወቀች ጊዜ እመቤቷን መናቅ ጀመረች። 5ሦራም አብራምን፣ “ለደረሰብኝ በደል ተጠያቂው አንተ ነህ፤ አገልጋዬ ዕቅፍህ ውስጥ እንድትገባ እኔው ሰጠሁህ፤ አሁን ግን ይኸው ማርገዟን ስታውቅ ትንቀኝ ጀመር፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) በአንተና በእኔ መካከል ይፍረድ” አለችው።

6አብራምም፣ “አገልጋይሽ እንደ ሆነች በእጅሽ ውስጥ ናት፤ የፈለግሽውን አድርጊባት” አላት። ከዚያም ሦራ ስላሠቃየቻት አጋር ጥላት ኰበለለች።

7የእግዚአብሔር (ያህዌ) መልአክ አጋርን በአንድ የውሃ ምንጭ አጠገብ በምድረ በዳ አገኛት፤ ምንጩም ወደ ሱር በሚወስደው መንገድ ዳር ነበር። 8መልአኩም፣ “የሦራ አገልጋይ አጋር ሆይ፤ ከየት መጣሽ? ወዴትስ ትሄጃለሽ?” አላት፤

እርሷም፣ “ከእመቤቴ ከሦራ ኰብልዬ መምጣቴ ነው” ብላ መለሰች።

9የእግዚአብሔርም (ያህዌ) መልአክ፣ “ወደ እመቤትሽ ተመለሽ፤ ለእርሷም ተገዥላት” አላት። 10ደግሞም መልአኩ፣ “ዘርሽን እጅግ አበዛለሁ፤ ከብዛቱም የተነሣ ሊቈጠር አይችልም” አላት።

11የእግዚአብሔርም (ያህዌ) መልአክ በተጨማሪ እንዲህ አላት፤

“እነሆ፤ ፀንሰሻል፤

ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ፤

እግዚአብሔር (ያህዌ) ችግርሽን ተመልክቷል፤

ስሙን እስማኤል16፥11 እስማኤል ማለት እግዚአብሔር ይሰማል ማለት ነው። ትዪዋለሽ።

12እርሱም እንደ ዱር አህያ ይሆናል፤

እጁንም ባገኘው ሰው ሁሉ ላይ ያነሣል፤

ያገኘውም ሁሉ እጁን ያነሣበታል፤

ከወንድሞቹ ሁሉ ጋር እንደ ተጣላ ይኖራል።”16፥12 ወይም በስተ ምሥራቅ ይኖራል

13እርሷም ያናገራትን እግዚአብሔርን (ያህዌ)፣ “ኤልሮኢ” ብላ ጠራችው፤ ምክንያቱም “የሚያየኝን አሁን አየሁት”16፥13 ወይም ኋላውን አየሁት ብላ ነበርና። 14ከዚህ የተነሣ የዚያ ምንጭ ስም፣ “ብኤርለሃይሮኢ”16፥14 ብኤርለሃይሮኢ ማለት የሚያየኝ የሕያው ምንጭ ማለት ነው። ተብሎ ተጠራ፤ እስካሁንም በቃዴስና በባሬድ መካከል ይገኛል።

15አጋር ለአብራም ወንድ ልጅ ወለደችለት፤ አብራምም ስሙን እስማኤል ብሎ ጠራው። 16አብራም፣ አጋር እስማኤልን በወለደች ጊዜ ዕድሜው 86 ዓመት ነበር።