Псалтирь 81 – NRT & NASV

New Russian Translation

Псалтирь 81:1-8

Псалом 81

1Псалом Асафа.

Бог возглавляет великое собрание81:1 Великое собрание – или: «собрание Бога».,

среди богов81:1 Или: «судей». Это слово на языке оригинала может означать «боги», «ангелы» и «судьи». Также в ст. 6. произносит суд:

2«Как долго еще вы будете судить несправедливо

и оказывать предпочтение нечестивым? Пауза

3Защищайте дело слабого и сироты,

угнетенному и бедному явите справедливость.

4Избавляйте слабого и нищего,

спасайте их от нечестивых.

5Их знание – ничто, их понимание бессмысленно.

Они ходят во тьме.

Содрогаются все основания земли.

6Я сказал: „Вы – боги,

все вы – сыны Всевышнего“

7но вы умрете, как все люди,

и вы падете, как любой из властителей».

8Восстань, Боже, и суди землю,

потому что Ты наследуешь все народы!

New Amharic Standard Version

መዝሙር 81:1-16

መዝሙር 81

ለዳስ በዓል የሚዜም ቅኔ

ለመዘምራን አለቃ፤ በዋሽንት የሚዜም፣ የአሳፍ መዝሙር።

1ብርታታችን ለሆነው አምላክ በደስታ ዘምሩ፤

ለያዕቆብ አምላክ እልል በሉ።

2ዝማሬውን ጀምሩ፤ ከበሮውን ምቱ፤

በበገናና በመሰንቆ ጥዑም ዜማ አሰሙ።

3በሙሉ ጨረቃ፣ በክብረ በዓላችን ዕለት፣

በወሩ መግቢያ፣ ጨረቃ ስትወለድ መለከት ንፉ፤

4ይህ ለእስራኤል የተሰጠ ሥርዐት፣

የያዕቆብም አምላክ ድንጋጌ ነውና።

5ሙሉ ለሙሉ ግብፅን ለቅቆ በወጣ ጊዜ፣

ይህን ለዮሴፍ ደነገገለት፤

በማላውቀውም81፥5 አንዳንዶች የማናውቀውን ድምፅ ሰማን ይላሉ። ቋንቋ እንዲህ ሲል ሰማሁ፤

6“ትከሻውን ከሸክም ገላገልሁት፤

እጁንም ቅርጫት ከመያዝ አሳረፍሁ።

7በመከራህ ጊዜ ጠራኸኝ፤ እኔም ታደግሁህ፤

በነጐድጓድ መሰወሪያ ውስጥ መለስሁልህ፤

በመሪባ ውሃ ዘንድ ፈተንሁህ። ሴላ

8“ሕዝቤ ሆይ፤ ሳስጠነቅቅህ ስማኝ፤

እስራኤል ሆይ፤ ምነው ብታደምጠኝ!

9በአንተ ዘንድ ባዕድ አምላክ አይኑር፤

ለሌላም አምላክ አትስገድ።

10ከግብፅ ምድር ያወጣሁህ፣

እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ነኝ፤

አፍህን በሰፊው ክፈተው፤ እኔም እሞላዋለሁ።

11“ሕዝቤ ግን አላደመጠኝም፤

እስራኤልም እጅ አልሰጥ አለኝ።

12ስለዚህ በገዛ ዕቅዳቸው እንዲሄዱ፣

አሳልፌ ለደንዳናው ልባቸው ሰጠኋቸው።

13“ምነው ሕዝቤ ቢያደምጠኝ ኖሮ፣

እስራኤል በመንገዴ በሄደ ኖሮ፣

14ጠላቶቻቸውን ፈጥኜ ባንበረከክኋቸው ነበር፤

እጄን በባላጋራዎቻቸው ላይ ባነሣሁ ነበር።

15እግዚአብሔርን የሚጠሉ በፊቱ ይርዳሉ፤

ቅጣታቸውም እስከ ዘላለም የሚዘልቅ ነው።

16እናንተን ግን ምርጡን ስንዴ አበላችኋለሁ፤

ከዐለቱም ማር አጠግባችኋለሁ።”