Псалтирь 46 – NRT & NASV

New Russian Translation

Псалтирь 46:1-10

Псалом 46

1Дирижеру хора. Псалом потомков Кораха.

2Рукоплещите, все народы,

вознесите Богу крик радости.

3Как грозен Господь Всевышний46:3 Евр.: «ЙГВГ Эльон».,

великий Царь над всей землей!

4Он покорил нам народы,

бросил нам под ноги племена.

5Он избрал нам наследие –

гордость Иакова, которого Он возлюбил. Пауза

6Бог вознесся под крики радости;

Господь вознесся под звуки рогов.

7Пойте Богу хвалу, пойте!

Пойте хвалу нашему Царю, пойте!

8Бог – Царь над всей землей;

пойте Ему искусный псалом46:8 Евр.: «маскил». Это слово можно означать «псалом размышления/наставления» или «мастерски написанные стихи»..

9Бог царит над народами;

Бог восседает на святом престоле Своем.

10Собираются вожди народов,

вместе с народом Авраамова Бога,

ведь земные правители46:10 Букв.: «щиты». принадлежат Богу;

Он высоко превознесся.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 46:1-11

መዝሙር 4646 ርእስ ምናልባት የሙዚቃውን ሁኔታ ሊያሳይ ይችላል።

እግዚአብሔር ከእኛ ጋር

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር፤ በደናግል የዜማ ስልት የሚዘመር መዝሙር።

1አምላካችን መጠጊያችንና ኀይላችን፣

በሚደርስብን መከራ ሁሉ የቅርብ ረዳታችን ነው።

2ስለዚህ ምድር ብትነዋወጥ እንኳ፣

ተራሮችም ወደ ባሕር ጥልቅ ቢሰምጡ አንፈራም።

3ውሆች ቢያስገመግሙ፣ ዐረፋ ቢደፍቁም፣ ተራሮችም ከውሆቹ ሙላት የተነሣ

ቢንቀጠቀጡም አንደናገጥም። ሴላ

4የእግዚአብሔርን ከተማ፣

የልዑልን የተቀደሰ ማደሪያ ደስ የሚያሰኙ የወንዝ ፈሳሾች አሉ።

5እግዚአብሔር በመካከሏ ነው፤ አትናወጥም፤

አምላክ በማለዳ ይረዳታል።

6ሕዝቦች በዐመፅ ተነሡ፤ መንግሥታትም ወደቁ፤

ድምፁን ከፍ አድርጎ አሰማ፤ ምድርም ቀለጠች።

7የሰራዊት አምላክ ከእኛ ጋር ነው፤

የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው። ሴላ

8ኑና የእግዚአብሔርን ሥራ፣

ምድርንም እንዴት ባድማ እንዳደረጋት እዩ።

9ከዳር እስከ ዳር ጦርነትን ከምድር ያስወግዳል፤

ቀስትን ይሰብራል፤ ጦርን ያነክታል፤

ጋሻንም46፥9 ወይም ሠረገላንም በእሳት ያቃጥላል።

10“ዕረፉ፤ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ ዕወቁ፤

በሕዝቦች ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ፤

በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ።”

11የሰራዊት አምላክ ከእኛ ጋር ነው፤

የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው። ሴላ