Псалтирь 115 – NRT & NASV

New Russian Translation

Псалтирь 115:1-10

Псалом 115

1Я верил, поэтому я и говорил:

«Я сильно сокрушен».

2В исступлении я сказал:

«Всякий человек – лжец».

3Чем воздам я Господу

за всю Его доброту ко мне?

4Возьму чашу спасения

и призову имя Господне.

5Исполню мои обеты Господу

перед всем Его народом.

6Дорога в глазах Господа

смерть верных Ему.

7Господи, истинно я – слуга Твой.

Я – слуга Твой и сын служанки твоей.

Ты освободил меня от цепей.

8Принесу Тебе жертву благодарности

и призову имя Господне.

9Исполню мои обеты Господу

перед всем Его народом,

10во дворах дома Господня,

посреди тебя, Иерусалим!

Аллилуйя!

New Amharic Standard Version

መዝሙር 115:1-18

መዝሙር 115

አንዱ እውነተኛው አምላክ

115፥4-11 ተጓ ምብ – መዝ 135፥15-20

1ለእኛ ሳይሆን፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ ለእኛ ሳይሆን፣

ስለ ምሕረትህና ስለ እውነትህ፣

ለስምህ ክብርን ስጥ።

2አሕዛብ፣ “አምላካቸው የት አለ?” ለምን ይበሉ?

3አምላካችንስ በሰማይ ነው፤

እርሱ ደስ የሚለውን ያደርጋል።

4የእነርሱ ጣዖታት ግን የሰው እጅ የሠራቸው፣

ብርና ወርቅ ናቸው።

5አፍ አላቸው፤ አይናገሩም፤

ዐይን አላቸው፤ አያዩም፣

6ጆሮ አላቸው፤ አይሰሙም፤

አፍንጫ አላቸው፤ አያሸትቱም፤

7እጅ አላቸው፤ አይዳስሱም፤

እግር አላቸው፤ አይሄዱም፤

በጕሮሯቸውም ድምፅ አይፈጥሩም።

8እነዚህን የሚያበጁ፣

የሚታመኑባቸውም ሁሉ እንደ እነርሱ ይሁኑ።

9የእስራኤል ቤት ሆይ፤ በእግዚአብሔር ታመኑ፤

ረዳታቸውና ጋሻቸው እርሱ ነው።

10የአሮን ቤት ሆይ፤ በእግዚአብሔር ታመኑ፤

ረዳታቸውና ጋሻቸው እርሱ ነው።

11እናንተ እግዚአብሔርን የምትፈሩ ሆይ፤ በእግዚአብሔር ታመኑ፤

ረዳታቸውና ጋሻቸው እርሱ ነው።

12እግዚአብሔር ያስበናል፤ ይባርከናልም፤

እርሱ የእስራኤልን ቤት ይባርካል፤

የአሮንንም ቤት ይባርካል።

13እግዚአብሔርን የሚፈሩትን ሁሉ፣

ትልቁንም ትንሹንም ይባርካል።

14እግዚአብሔር እናንተንና ልጆቻችሁን፣

በባርኮቱ ያብዛችሁ።

15ሰማይንና ምድርን በፈጠረ፣

በእግዚአብሔር የተባረካችሁ ሁኑ።

16ሰማየ ሰማያት የእግዚአብሔር ናቸው፤

ምድርን ግን ለሰው ልጆች ሰጣት።

17እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑት የሞቱት አይደሉም፤

ወደ ዝምታው ዓለም የሚወርዱም አይደሉም።

18ከአሁን ጀምሮ እስከ ዘላለም፣

እግዚአብሔርን የምንባርክ እኛ ነን።

እግዚአብሔር ይመስገን።115፥18 ዕብራይስጡ ሃሌ ሉያ ይላል።