Псалтирь 112 – NRT & NASV

New Russian Translation

Псалтирь 112:1-9

Псалом 112

1Аллилуйя!

Воздайте хвалу Господу, слуги Господни,

воздайте хвалу имени Господа!

2Да будет прославлено имя Господне

отныне и вовеки!

3От востока и до запада112:3 Букв.: «От восхода солнца и до заката».

да будет прославлено имя Господне!

4Господь превознесен над всеми народами,

и слава Его выше небес.

5Кто подобен Господу, нашему Богу,

восседающему на троне в вышине?

6Он склоняется, чтобы взирать

на происходящее на небе и на земле.

7Он поднимает бедного из праха

и возвышает нищего из грязи,

8чтобы посадить их с вождями,

с вождями их народа.

9Бесплодную женщину вселяет в дом

счастливой матерью.

Аллилуйя!

New Amharic Standard Version

መዝሙር 112:1-10

መዝሙር 112

የጻድቅ ሰው ባሕርይ

1ሃሌ ሉያ።112፥1 እግዚአብሔር ይመስገን ማለት ነው።

እግዚአብሔርን የሚፈራ፣

በትእዛዙም እጅግ ደስ የሚሰኝ የተባረከ ነው።

2ዘሩ በምድር ላይ ኀያል ይሆናል፤

የቅኖች ትውልድ ትባረካለች።

3ሀብትና ብልጽግና በቤቱ ይሞላል፤

ጽድቁም ለዘላለም ይኖራል።

4ቸር፣ ርኅሩኅና ጻድቅ እንደ መሆኑ፣

ለቅን ሰው በጨለማ ውስጥ ብርሃን ይወጣለታል።

5ለጋስና ያለ ማንገራገር የሚያበድር፣

ሥራውንም በትክክል የሚያከናውን ሰው መልካም ይሆንለታል፤

6ለዘላለም ከስፍራው አይናወጥምና፤

ጻድቅ ሰው ሲታወስ ይኖራል።

7ክፉ ወሬ አያሸብረውም፤

ልቡ እግዚአብሔርን በመተማመን የጸና ነው።

8ልቡ የጸና ነው፤ አይፈራምም፤

በመጨረሻም የጠላቶቹን ውድቀት ያያል።

9በልግስና ለድኾች ሰጠ፤

ጽድቁ ለዘላለም ይኖራል፤

ቀንዱም112፥9 በዚህ ስፍራ ክብርን ያመለክታል። በክብር ከፍ ከፍ ይላል።

10ክፉ ሰው ይህን በማየት ይበሳጫል፤

ጥርሱን ያፋጫል፤ እየመነመነም ይጠፋል፤

የክፉዎችም ምኞት ትጠፋለች።