Zechariah 13 – NIV & NASV

New International Version

Zechariah 13:1-9

Cleansing From Sin

1“On that day a fountain will be opened to the house of David and the inhabitants of Jerusalem, to cleanse them from sin and impurity.

2“On that day, I will banish the names of the idols from the land, and they will be remembered no more,” declares the Lord Almighty. “I will remove both the prophets and the spirit of impurity from the land. 3And if anyone still prophesies, their father and mother, to whom they were born, will say to them, ‘You must die, because you have told lies in the Lord’s name.’ Then their own parents will stab the one who prophesies.

4“On that day every prophet will be ashamed of their prophetic vision. They will not put on a prophet’s garment of hair in order to deceive. 5Each will say, ‘I am not a prophet. I am a farmer; the land has been my livelihood since my youth.13:5 Or farmer; a man sold me in my youth6If someone asks, ‘What are these wounds on your body13:6 Or wounds between your hands?’ they will answer, ‘The wounds I was given at the house of my friends.’

The Shepherd Struck, the Sheep Scattered

7“Awake, sword, against my shepherd,

against the man who is close to me!”

declares the Lord Almighty.

“Strike the shepherd,

and the sheep will be scattered,

and I will turn my hand against the little ones.

8In the whole land,” declares the Lord,

“two-thirds will be struck down and perish;

yet one-third will be left in it.

9This third I will put into the fire;

I will refine them like silver

and test them like gold.

They will call on my name

and I will answer them;

I will say, ‘They are my people,’

and they will say, ‘The Lord is our God.’ ”

New Amharic Standard Version

ዘካርያስ 13:1-9

ከኀጢአት መንጻት

1“በዚያ ቀን የዳዊትን ቤትና የኢየሩሳሌምን ነዋሪዎች ከኀጢአትና ከርኩሰት የሚያነጻ ምንጭ ይከፈታል።

2“በዚያ ቀን የጣዖታትን ስም ከምድሪቱ አጠፋለሁ፤ ከእንግዲህም አይታሰቡም” ይላል እግዚአብሔር ጸባኦት። “ነቢያትንና ርኩስ መንፈስን ከምድሪቱ አስወግዳለሁ። 3ማንም ትንቢት ቢናገር ወላጅ አባትና እናቱ፣ ‘በእግዚአብሔር ስም ሐሰት ተናግረሃልና ሞት ይገባሃል’ ይሉታል። ትንቢት ሲናገርም የገዛ ወላጆቹ ይወጉታል።

4“በዚያን ቀን እያንዳንዱ ነቢይ ስለሚናገረው የትንቢት ራእይ ያፍራል፤ ለማታለልም የነቢያትን ጠጕራም ልብስ አይለብስም። 5እርሱም፣ ‘እኔ ገበሬ እንጂ ነቢይ አይደለሁም፤ ከልጅነቴ13፥5 ወይም ዐራሽ፤ በወጣትነቴ የተሸጥሁ ሰው ጀምሮ ኑሮዬ የተመሠረተውም በዕርሻ ላይ ነው’ ይላል። 6አንድ ሰው፣ ‘ይህ በሰውነትህ13፥6 በእጆችህ መኻል ያሉ ቍሰሎች የሚሉ አሉ። ላይ ያለው ቍስል ምንድን ነው?’ ብሎ ቢጠይቀው፣ ‘በባልንጀሮቼ ቤት ሳለሁ የቈሰልሁት ነው’ ይላል።”

እረኛው ተመታ፤ በጎቹ ተበተኑ

7እግዚአብሔር ጸባኦት እንዲህ ይላል፤

“ሰይፍ ሆይ፤ በእረኛዬ፣

በቅርብ ወዳጄ ላይ ንቃ!

እረኛውን ምታ፣

በጎቹ ይበተናሉ፤

እኔም ክንዴን ወደ ታናናሾቹ አዞራለሁ።”

8እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ “የምድር ሁሉ፣

ሁለት ሦስተኛው ተመትቶ ይጠፋል፤

አንድ ሦስተኛው ግን በውስጡ ይቀራል፤

9ይህን አንድ ሦስተኛውን ክፍል ወደ እሳት አመጣለሁ፤

እንደ ብር አነጥራቸዋለሁ፤

እንደ ወርቅም እፈትናቸዋለሁ፤

እነርሱ ስሜን ይጠራሉ፤

እኔም እመልስላቸዋለሁ፤

እኔም፣ ‘ሕዝቤ ናቸው’ እላለሁ፤

እነርሱም፣ ‘እግዚአብሔር አምላካችን ነው’ ይላሉ።”