Job 11 – NIV & NASV

New International Version

Job 11:1-20

Zophar

1Then Zophar the Naamathite replied:

2“Are all these words to go unanswered?

Is this talker to be vindicated?

3Will your idle talk reduce others to silence?

Will no one rebuke you when you mock?

4You say to God, ‘My beliefs are flawless

and I am pure in your sight.’

5Oh, how I wish that God would speak,

that he would open his lips against you

6and disclose to you the secrets of wisdom,

for true wisdom has two sides.

Know this: God has even forgotten some of your sin.

7“Can you fathom the mysteries of God?

Can you probe the limits of the Almighty?

8They are higher than the heavens above—what can you do?

They are deeper than the depths below—what can you know?

9Their measure is longer than the earth

and wider than the sea.

10“If he comes along and confines you in prison

and convenes a court, who can oppose him?

11Surely he recognizes deceivers;

and when he sees evil, does he not take note?

12But the witless can no more become wise

than a wild donkey’s colt can be born human.11:12 Or wild donkey can be born tame

13“Yet if you devote your heart to him

and stretch out your hands to him,

14if you put away the sin that is in your hand

and allow no evil to dwell in your tent,

15then, free of fault, you will lift up your face;

you will stand firm and without fear.

16You will surely forget your trouble,

recalling it only as waters gone by.

17Life will be brighter than noonday,

and darkness will become like morning.

18You will be secure, because there is hope;

you will look about you and take your rest in safety.

19You will lie down, with no one to make you afraid,

and many will court your favor.

20But the eyes of the wicked will fail,

and escape will elude them;

their hope will become a dying gasp.”

New Amharic Standard Version

ኢዮብ 11:1-20

ሶፋር

1ነዕማታዊው ሶፋር እንዲህ ሲል መለሰ፤

2“ይህ ሁሉ ቃል መልስ ማግኘት አይገባውምን?

ወይስ ተናጋሪ ሰው እንደ እውነተኛ ይቈጠርን?

3በውኑ የአንተ መዘላበድ ሰውን ዝም ያሰኛልን?

ስታፌዝስ የሚገሥጽህ የለም?

4እግዚአብሔርንም፣ ‘ትምህርቴ የጠራ፣

በዐይንህም ፊት የጸዳሁ ነኝ’ ትለዋለህ።

5ምነው እግዚአብሔር ቢናገርህ!

ከንፈሩንም በአንተ ላይ ቢከፍት!

6እውነተኛ ጥበብ ባለ ብዙ ፈርጅ ናትና፣

የጥበብንም ምስጢር ምነው በገለጠልህ!

እግዚአብሔር ለኀጢአትህ የሚገባውን እንዳላስከፈለህ ባወቅህ ነበር።

7“የእግዚአብሔርን ጥልቅ ምስጢር ልትለካ ትችላለህን?

ወይስ ሁሉን የሚችለውን አምላክ መርምረህ ትደርስበታለህን?

8ከሰማይ ይልቅ ከፍ ይላል፤ ምን ልታደርግ ትችላለህ?

ከሲኦልም11፥8 ወይም ከመቃብር ይጠልቃል፤ ምን ልታውቅ ትችላለህ?

9መጠኑ ከምድር ይልቅ ይረዝማል፤

ከባሕርም ይልቅ ይሰፋል።

10“እርሱ ተከታትሎ መጥቶ በግዞት ቢያስቀምጥህ፣

የፍርድ ሸንጎም ቢሰበስብ፣ ማን ሊከለክለው ይችላል?

11በእውነት እርሱ ሸፍጠኞችን ያውቃል፣

ክፋት ሲሠራም ልብ ይላል።

12ጅል ሰው ጥበበኛ ከሚሆን ይልቅ፣

የሜዳ አህያ ሰው ሆኖ ቢወለድ ይቀላል።11፥12 ወይም የዱር አህያ ለማዳ ሆኖ ሊወለድ ይችላል

13“ነገር ግን ልብህን ብትሰጠው፣

እጅህንም ወደ እርሱ ብትዘረጋ፣

14በእጅህ ያለውን ኀጢአት ብታርቅ፣

ክፋትም በድንኳንህ እንዳይኖር ብታደርግ፣

15በዚያን ጊዜ ሳታፍር ቀና ትላለህ፤

ያለ ፍርሀት ጸንተህ ትቆማለህ፤

16መከራህን ትረሳለህ፤

ዐልፎ እንደ ሄደ ጐርፍም ታስበዋለህ።

17ሕይወትህ ከቀትር ይልቅ ያበራል፤

ጨለማውም እንደ ንጋት ይሆናል።

18ተስፋ ስላለ ተደላድለህ ትቀመጣለህ፤

ዙሪያህን ትመለከታለህ፣ በሰላምም ታርፋለህ።

19ያለ አንዳች ሥጋት ትተኛለህ፤

ብዙ ሰዎችም ደጅ ይጠኑሃል።

20የክፉዎች ዐይን ግን ትጨልማለች፤

ማምለጫም አያገኙም፤

ተስፋቸውም ሞት ብቻ ነው።”